Friday, April 3, 2015

በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!

Posted by Yeharerwerk Gashaw


'እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ
የመን ባለ ስደተኛ ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!! የገንዘብ እርዳታ አንፈልግም
       በግሩም ተ/ሀይማኖት
    የመን ባለችበት ችግር ውስጥ ኢትየጦጵያዊያን እያዩ ያሉት ስቃይ አሁን ብሶ ነው ያለው፡፡ ባለፈው ሰኞ ሀረድ የተባለ ቦታ መዝረቅ የተባለ የስደተኞች  ካምፕ የአየር ጥቃት ደርሶበት 46 ሰው ሞተ ብዬ ጽፌያለሁ፡፡ ይህን በተመለከተ አንድ አነስተኛና ጥቃቅን ስድብ አምራች የቻለውን ያህል ለመሳደብ ሞክሯል፡፡ እውነታው ግን  ያስጨነቃቸውም፣ እንዲሳደቡ ያደረጋቸውም በተለያየ ቦታ በስደተኛው ስም  ገንዘብ ለመሰብሰብ ቋምጠው የነበሩ ናቸው፡፡ በተለያየ ሚዲያ የመን ላለ ስደተኛ አሁን የሚያስፈልገው ህይወቱን የሚያድንበት መፍትሄ እንጂ ገንዘብ አለመሆኑን ደጋግሜ በመናገሬ መንገዱ ስለተዘጋባቸው ነው፡፡  አሁንም ደግሜ ደግሜ የምገልጸው የመን ያለ ስደተኛ ሀገሪቷ በአየር ድብደባ እየተደረገባት በመሆኑ ስደተኛው ላይ ሊደርስ የሚችለውን አስቦ የህይወት ማዳን ተግባር ከወገኖቹ ይጠብቃል እና ኢትዮጵያዊ ነን ያላችሁ በጦርነት መካከል UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ታደጉት ነው ጥሪዮ፡፡ በተለያየ መገናኛ ብዙሀን እንደተናገርኩት አሁንም እደግመዋለሁ UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ነፍስ ታደጉት፡፡ ለጊዜው የመን ያለ ስደተኛ የገንዘብ የምግብ ወይም መሰል ችግር አልገጠመውም እና ገንዘብ አሰባስቡ ለሚሏችሁ ገንዘባችሁን እንዳታወጡ፡፡ ለበላተኛ እንዳትሰጡ፡፡ ችግር ሲኖር ወቅቱን ጠብቆ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ ስለዚህ ጥቅማቸው የተነካ ሰዎች ሲሳደቡ ተቆጭታችሁ መልስ አትስጡ ያጣ ለማኝ ይሳደባል ነው ነገሩ፡፡ እንዲያውም እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ፡፡ በእኔ በኩል ግን ያለኝ መልስ ‹‹..ውሻ ጮኸ ብሎ የሚጮህ ቢኖር ውሻ ነው…›› የሚል ነው፡፡ እባካችሁ ለችግር ጊዜ ከተማራችሁት ስድብ ደጋግሙኝ….በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!'



20 hrs · 
፡ አሁንም ደግሜ ደግሜ የምገልጸው የመን ያለ ስደተኛ ሀገሪቷ በአየር ድብደባ እየተደረገባት በመሆኑ ስደተኛው ላይ ሊደርስ የሚችለውን አስቦ የህይወት ማዳን ተግባር ከወገኖቹ ይጠብቃል እና ኢትዮጵያዊ ነን ያላችሁ በጦርነት መካከል UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ታደጉት ነው ጥሪዮ፡፡ በተለያየ መገናኛ ብዙሀን እንደተናገርኩት አሁንም እደግመዋለሁ UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ነፍስ ታደጉት፡፡ ለጊዜው የመን ያለ ስደተኛ የገንዘብ የምግብ ወይም መሰል ችግር አልገጠመውም እና ገንዘብ አሰባስቡ ለሚሏችሁ ገንዘባችሁን እንዳታወጡ፡፡ ለበላተኛ እንዳትሰጡ፡፡ ችግር ሲኖር ወቅቱን ጠብቆ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ ስለዚህ ጥቅማቸው የተነካ ሰዎች ሲሳደቡ ተቆጭታችሁ መልስ አትስጡ ያጣ ለማኝ ይሳደባል ነው ነገሩ፡፡ እንዲያውም እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ፡፡ በእኔ በኩል ግን ያለኝ መልስ ‹‹..ውሻ ጮኸ ብሎ የሚጮህ ቢኖር ውሻ ነው…›› የሚል ነው፡፡ እባካችሁ ለችግር ጊዜ ከተማራችሁት ስድብ ደጋግሙኝ….በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!

ግሩም ተክለሃይማኖት የኢትዮጵያ ስዴተኞች በየመን እና ኢትዮጵያውያን በአረብ አገር ኮሚቲ ሊቀመንበር ሳና የመን።
Like · Comment ·