Thursday, April 23, 2015

Worldwide Ethiopian Refugees' Advocate Group የኢትዮጵያ ስዴተኞችን አስመልክቶ ጥበቃ እንዲደረገላቸው ከሊቢያ መንግስት ጋር መነጋገር ጀምርዋል።

Worldwide Ethiopian Refugees' Advocate Group
Dallas, Texas USA (Founded in 1983 in Dallas, Texas)
Phone # 214-642-0394
email: yehar9@aol.com

አጭር መግለጫ
April 21, 2015

 Worldwide Ethiopian Refugees' Advocate Group የኢትዮጵያ ስዴተኞችን አስመልክቶ ጥበቃ እንዲደረገላቸው ከሊቢያ መንግስት ጋር መነጋገር ጀምርዋል

     በኢትዮጵያ ስዴተኞች ላይ የደረሰውን የግፍ ግዲያ በጥብቅ እንቃወማለን። ግፈኞችም ወደ ፍርድ ተፈልገው እንዲቀርቡ ሰላም ወዳድ የአለም ሕዝብ እንዲተባበርም እናሳስባልን። 

    አሁንም ግድያውን ለመድገም ግፈኛው ፋሽስቱ አይሰስ ወደ ሁዋላ እንዳላለም በመገንዘችን በሊብያ መንግስት በኩል በተለይ ኢትዮጵያውያን ስዴተኞችን ላይ በሊቢያ ወታደሮች እና ፓሊሶች በግፍ እየተያዙ መታሰር እና መደብደብ ከዛም አሳልፈው ለአይሰስ መስጠታቸውን እንዲያቁሙ የሊያን መንግስት ማለትም በአለም መንግስታት በመንግስትነት ተቀባይነት ያለውን ቀርቦ ከማነጋገር ሌላ ምንም መፍትሄ የለም :: ስለሆነም አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ስዴተኞች መብት ተከራካሪ እና ጉዳይ አስፈጻሚ ስብስብ (Worldwide Ethiopian Refugees' Advocate Group founded in 1986) ንዋሪነቱ በዳላስ ቴክሳስ አሜሪካ : ከሊብያ መንግስት ጋር እየተነጋገረ ይገል።


      እንደሚታወቀው በአሁን ጊዜ ሊብያ ሁለት ሃይል ነው የያዛት። ሆኖም በአለም መንግስታት እና ሕዝብ በሃያሉም መንግስትነትም በአሜሪካን እውቅና ካለው የሊቢያ መንግስት ተወካዮች ጋር አምባሳደር ኢብራሂም ደባሺ እና ሌሎች ዲፕሎማቲኮችን በመጨመር በኢትዮጵያ ስዴተኞች ላይ የሊቢያ ወታደሮች እያደንዋቸው እናም ለአይሰስ አሳልፈው እየሰጥዋቸው በመሆኑ መንግስታቸውን አምባሳደሩ እና በጉዳይ አስፈጸሚነት የተቀመጡትን ጭምር አንደኛ ወታደሮቻቸው ኢትዮጵያውያንን ከሚኖሩበት እየወሰዱ በእስር ቤት ውስጥ በማጨቅ የሚደረገው እስራት እንዲቆም እና ለአይሰስም አሳልፈው መስጠታቸውን እንዲያቆሙ በሰራዊቱም ይሁን ፓሊስ መንግስትነት የሚታወቀው አካል ከማንኛውም ጥቃት እንዲከላከልላቸው ጥበቃ እንዲደረገላቸው ዛዝ እንዲሰጥ እና እንዲተባበረን ግልጽ ደብዳቤ አቅርበናል::  ከሶስት ቀን በፊትም በጉልበት የተወሰዱ ኢትዮጵያውያን ስላሉ ከተያዙበት ባስቸክዋይ እንዲለቀቁ። ኢትዮጵያውያንን ክርስቲያኖችን በግፍ ለመግደል ለአይሰስ በቀላሉ እንዲያመቼው መንገድ የከፈተለት በግፍ እንደወንጀለኛ እየታሰሩ ወደ እስር ቤት በመጣላቸው ስለሆነ ባስቸኩዋይ የልቢያ መንግስት ያሰራቸውን እንዲፈታ። አይሰስም ክርስቲያን በመሆናቸው ወስዶ በግፍ የሞት ቅጣት የፈጸመባቸውን  ኢትዮጵያውያንንም ማን አሳልፎ እንደሰጣቸው እና እንዴትስ ለሞት ሊዳረጉ እንደተደረገ መልስ ከሊብያ መንግስት ይሰጠን በሚል ጭምር ጠይቀናል። ስለሆነም ሌላውም ኢትዮጵያዊ እና መላው ሕዝባችን ይሄንን መግለጫ ያገኘ ሁሉ ከስር ባስቀመጥነው የአምባሳደሩ እና የጉዳይ አስፈጻሚው የኢሜል አድራሻ እንዲሁም ስልክ ቁጥር በመጠቀም የኢትዮጵያ ስዴተኞች ወደ እስር ቤት መወር ወር እና በሊብያ ፓሊሶች እና ወታደሮች እየታደኑ ለአደጋ በእስር ቤትም ይሁን በማንናውም ቦታ እንዳያጉርዋቸው የሊብያ መንግስት እንዲተባበርን በትህትና እንድታሳስቡ በአለም አቀፍ የኢትዮጵያ ስዴተኞች መብት ተከራካሪ እና ጉዳይ አስፈጻሚ ስብስብ ስም እንዲሁም በራሴ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼን አሳስባለሁ። 

የሐረርወርቅ-የኢትዮጵያወርቅ ጋሻው።
መስራችና ሊቀመንበር።


Ambassador ኢብራሂም ደባሺ (Dabbashi), in New York, svc.libyamission@gmail.com
Phone # 212-752-5775.
Libyan Charge d' affairs Mr. Wafa Bugaighis in washington D.C. aujalimedia@gmail.com
Phone # 202-944-9601

Sunday, April 12, 2015

ስደተኛው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት፤ የየመን ቀውስ በኢትዮጵያውያን ስደተኞችና መጤ ሠራተኞች ላይ ስላሳደረው ተፅእኖ ይናገራል።

Posted by Yeharerwerk Gashaw

                                         https://www.youtube.com/watch?v=2rsv_ck4uyw
SBSAmharic

Interview with Journalist Girum Teklehaymanot -
By Journalist Kassahun Seboqa,
SBS Amharic News

Monday, April 6, 2015

Ethiopian Refugees In Yemen Appoint Actress & Human Rights Activist Yeharerwerk Gashaw As International Representative.

Ethiopian Refugees In Yemen

‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ ግሩፕ›› መስራችና የየመን ስደተኞች ኮሚቴ
ግሩም ተ/ሀይማኖት::
ግልጽ መግለጫ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ
ጉዳዩ፡- የመን ያሉ ኢትዮጵያዊን ስደተኞች ችግር
በአረቡ አለም ላይ የተነሳውን አብዮት ተከትሎ የመን እስካሁን በጦርነት ስትማቅቅ ስደተኛውም ሲማቅቅ ከርሟል፡፡ከ2011 ጀምሮ ሞቅ በረድ የሚለው የእርስ በእርስ ጦርነት ስደተኛውንም ሲያሞቅ ሲያቃጥለው እዚህ ደርሷል፡፡ አሁን ተቃዋሚው የሁቲይ አማጺ ሚሊሻ ከፊል ሀገሪቱን ተቆጣጥሮ ሳለ በሳዑዲ አረቢያ አስተባባሪነት ስምንት ሀገሮች ካለፈው ሀሙስ 26/3/15 ጀምሮ የአየር ጥቃት እየሰነዘሩ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዜጎቼን ወደ ሀገሬ አስገባለሁ ብሎ መመዝገብ ጀምሯል፡፡ ወደ ሀገር መግባት የማይችሉ የፖለቲካና የተለያየ ችግር ያለባቸው በUNHCR ስር የስደተኛነት ማረጋገጫ ወረቀት (Mandate) ይዘው ያሉት ግን በጭንቅ ውስጥ ናቸው፡፡ መጨረሻዬ ምን ይሆን? በሰው ሀገር የሚለው ጥያቄ መልስ አልባ ሆኖባቸዋል፡፡ 

ጭንቅ ውስጥ ያስገባቸው የUNHCR ቢሮ ስደተኛውን ምንም ሳያደርግለት በትኖ ቢሮውን ዘግቶ በመውጣቱ ነው፡፡ 4000 ኢትዮያዊያን እና 1000 ኤርትራዊያን ስደተኞችን ምንም አይነት ከለላ ሳይሰጥ ሰራተኞቹን ብቻ ይዞ በመውጣቱ ስደተኛው ተስፋ ቆርጦ ሞቱን መጠባበቅ እጣ ፋንታው ሆነ፡፡ አሁን በየመን ይህን መሰል ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ይግጠም እንጂ በመላው አረብ ሀገራት ኢትዮጵያዊያን በስቃይ እና ተረግጠው፣ ተገፍተው ነው የሚኖሩት፡፡ ይህ በመሆኑ ችግራቸውን የሚፈታላቸው ጥቃት ሲደርስባቸው፣ ሲጎዱ ሲታመሙ የተለያየ ችግር ሲገጥማቸው አይዟችሁ የሚል ወገንም መንግስትም የላቸውም፡፡ ለምን ይሄ ተደረገባቸው? ለምን መብታቸው ተጣሰ? የሚል ባለመኖሩ የማንም መጫወቻ በመሆናቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያን ራሳቸው ያጠፋሉ፡፡ ታመው ወድቀው በዛው ይቀራሉ፡፡ በየሆስፒታሉ ሬሳቸው መጫወቻ እየሆነ ፍሪጅ ውስጥ ይቀራል፡፡ ታመው አስታማሚ በማጣት ችግሩ ይከፋባቸዋል፡፡ 

በፈርጅ ብዙ ችግር የታጠረው ኢትዮጵያዊ ስደተኛን ማንም ዞር ብሎ የሚያየው እኔ አለሁህ የሚለው ታጣ፡፡ በአረብ ሀገራት ያሉትን ስደተኞች ችግር በአምስት አመት በላይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል ወገኖቻችን እንዲሰሙ አደረኩኝ፡፡ ለወገን ተቆርቋሪ ነን ኢትዮጵያን እንወዳታለን የሚሉትን ሁሉ ‹‹ጎበዝ ወገን ረገፈ፣ ወገን ባህር በላው፣ወገኖቻችን ኤጀንሲዎች በዘመናዊ ባርነት ሸጧቸው፣ ኤምባሲውም ረሳቸው…ያላልኩት የለም፡፡ ለካ ኢትዮጵያን እንወዳታለን የሚለው ሁላ ኢትዮጵያን አፈርና ድንጋዩን ብቻ ነው የሚወዱት ህዝቡን አይፈልጉትም እስክል ድረስ በዝምታቸው ውስጥ ሰመጡ፡፡ 

ድረ-ገጾችም (ዌብ ፔጆችም) እነሱ በሚነፍሱበት አቅጣጫ የሚያራግብ መልዕክት ካልሆነ ስለስደተኛው አጀንዳቸው አይደለምና ገጻቸው ላይ መለጠፉን አይፈቅዱም፡፡ ሰሚ ጠፋ፡፡ ያለኝ አማራጭ አንድና አንድ ሆነና ‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊ ስደተኞችን መብት ጥሰት ድምጽ እናሰማ›› የሚል ላይክ ገጽ ከፈትኩ፡፡ በዛ ገጽ እና በዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ያሰባሰብኳቸውን ልጆች በማስተባበር ‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ ግሩፕ›› በዋትስአፕ አቋቋምኩኝ፡፡ በዚህ ግሩፕ ስር የበርካታ ልጆችን ችግር መፍታት ቻልን፡፡ ባለፈው ሀሙስ የመን ላይ የተጀመረውን የአየር ጥቃት ተከትሎ UNHCR ቢሮውን ጭርሱኑ ዘግቶ ሲወጣ እዚሁ ግሩፕ ላይ ተወያየንበት፡፡ ለመፍትሄ ያቀረብነው ሀሳብም የመን ካሉት ስደተኞች ውስጥ መሰባሰብ የሚችሉትን አሰባስቦ ኮሚቴ በማዋቀር ከውጭ ሊንቀሳቀሱልን የሚችሉ እንደ ከዚህ ቀደሙ አለን አለን ብለው መረጃችንን ወስደው መነገጃ የማያደርጉን ሰዎች መፈለግ እንዳለብን ወሰንን፡፡ ይህን ውሳኔ ተከትሎ እኔም በነጻ ፕሬስ ውስጥ ለሀገሬ የመናገር ነጻነት የታገልኩትን ረስተው የሚቶፍዝልኝ አጥቼ የመን መክረሜን አስመልክቼ ‹‹ግሩምዬ ያንተስ መጨረሻ ምንድን ነው?›› የሚል ርዕስ ሰጥቼ መረር ያለ መጣጥፍ ፌስቡክ ገጼ ላይ ለጠፍኩ፡፡

ወዲያው የሀረርወርቅ ጋሻው ምላሽ ሰጠችኝ፡፡ የቀድሞ ባህር ሀይሎች እና ከጅቡቲ አየር ሀይሎችን ወደ ሶስተኛ ሀገር ለማሻገር ያደረገችውን ትግል ሰምቼ ነበር፡፡ ከተወሰኑ የቀድሞ ባህር ኃይል እና አየር ሀይል ባልደረባዎች ጋር ተነጋገርኩ፡፡ ያንኑ ሀሳብ ‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ የዋትስአፕ ግሩፕ ላይ እና ለተሰባሰብነው የየመን ስደተኛዎች ኮሚቴ አቀረብኩ፡፡ ከየሀረርወርቅ ጋሻው ጋር ባለን ግንኙነት ላይ ተስማማን ወከልናትም፡፡ ሌሎችም ወገኖቻችን በየመን የከፋ አደጋ እንዳያጋጥማቸው ያላችሁ በጋራ ሰርታችሁ ካለንበት ህይወትና ሞት አጣብቂኝ ውስጥ እንድንወጣ ብታደርጉ ኢትዮጵያ ከእናንተ የምትፈልገውን ፍቅር መስጠታችሁ ብቻ ሳይሆን የአእምሮም፣ የህሊናም እርካታ ይሆናችኋል፡፡
‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ ግሩፕ›› መስራችና የየመን ስደተኞች ኮሚቴ
ግሩም ተ/ሀይማኖት::

Sunday, April 5, 2015

የኮሚቲ ስም ዝርዝር (የመን የሚገኘው የኢትዮጵያ ስዴተኞች አለም አቀፍ ጉዳይ አስፈጻሚ እና የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቲ ዳላስ ቴክሳስ ዩኤስኤ:)

                                                                                             
ይድረስ በየመን ለሚገኘው የኢትዮጵያ ስዴተኞች ኮሚቲ ሊቀመንበር አቶ ግሩም ተክለሃይማኖት
እና ስለስዴተኛው ከልቡ ለሚቆረቆረው የኢትዮጵያ ሕዝብ።

 እንድታውቁት ያህል
April 5, 2015

ክዚህ በታች ስማቸው በከፊል ተጽፎ የሚገኘው፡ (በተለያዩ አገሮች የኢትዮጵያን ስዴተኞች ፡ የስዴተኛነት መብታቸው ተከብሮ ተቀባይነት እንዲኖራቸው እና ካሉበትም ከአፍሪካ፡ ከመካከለኛ ምስራቅ ወደ አውሮፓ ፡ አሜሪካን ካናዳ እናም አውስትራልያ ተቀባይነት እድኒኖራቸው ለማደርገው ትግል እንደያስፈላጊነቱ እጎኔ ቆመው የስዴተኛውን ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችንን ጉዳይ አስመልክቶ በስራ የሚተባበሩኝ)የኮሚቲ አባላት ናቸው።  ስለሆነም በአሁን ጊዜ የመን የሚገኘውን ኢትዮጵያዊ ስዴተኛ ጉዳይ አስመልክቶ ወደ አራት አገሮች ተቀባይነት እንዲያገኙ በቅርብ የጀመርኩትን ተግባር አብረውኝ ለመስራት ቆርጠው መነሳታቸውን እና በጉዳዩም እኔም እነሱም በትናንትናው ምሽት ሳይቀር በስልክ ቅደም ተከተሉን የነደፍኩትን ስልት ለ5000 ሺ ስዴተኞች ይረዳ ዘንድ ባቀረብኩላቸው መሰረት ተቀብለውት እነሱም የበኩላቸውን አስበውበት ጠቃሚውን ሁሉ ሃሳብ አክለውበት ባስቸኩዋይ በኤሜል ሊልኩ ተስማምተን ስራው በእኔ ብቻ ሳይሆን በኮሚቲው ጭምር ተጀምርዋል።

ከኮሚቲው አባላት መሃል ከአቶ ነብዩ ዳምጤ የቀረበ ሃሳብ አለ ። ይሄውም ለሚመለከተው ሁሉ ብሎም የኢትዮጵያ ሕዝብ ስዴተኛው ያለበትን ሁኔታ በበለጠ ይረዳው እንዲችል ስዴተኞቹ ያሉበትን ስቃይ ፡ ከተቻለ ከስዴተኞቹ መሃል የተወሰኑትን ቃለመጠየቅ በቬዲዮ እራሱ አቶ ግሩም እንዲጠይቃቸው ቢያደርግ ለምንሰራውም የስዴተኛውን ጉዳይ ማስፈጸም እንደሚረዳን እና እንደዚህ መከራ እንደበረዶ እየዘነበባቸው ያለውን ወገኖቻችን የኢትዮጵያም ሕዝብ ተመልክቶ እያንዳንዱ በቀጥታ ለባለጉዳዮቹ በኮሚቲያቸው በኩል በጎአድራጎት እንዲያደርግም ይረዳል በሚል አሳስበዋል።

ጋዜጠኞች።
እንደምታወቀው ታዋቂነት ያላቸው የአሜሪካን አገር እና የሌሎቹም አገሮች ጋዜጠኞች እራሳቸው ትልቅ እርዳታ ናቸው። ስለሆነም በየመን ያለውን በአቶ ግሩም ሊቀመንበርነት የሚመራውን እና እኛም የምንመራው ውስጥ በናኡስ ኮሚቲነት የሚተባበሩንን አካተናል:: ከአክብሮት ጋር
የኢትዮጵያወርቅ-የሐረርወርቅ ጋሻው
ሊቀመንበር።

ኮሚቲ ስም፡
የኢትዮጵያውርቅ-የሐረርወርቅ ጋሻው።
ዶክተር ማንከልክሎት ሃይለስላሴ ዋሽንግተን ዲሲ።
ዶክተር ጋሹ ሃብቴ አርካንሳስ።
አቶ ብዩ ዳምጤ ዳላስ ቴክሳስ።
አቶ መሰለ ከለ ዳላስ ቴክሳስ።
ዶክተር አበባ ፈቃደ ዋሺንግተን ፡ዲሲ::
ዶክተር ተዘራ ጸጋዬ አትላንታ።
ወይዘሮ ጸሃይ በቀለ አትላንታ።
ዶክተር አረጋህኝ ሴፉ መንፊስ።
ወይዘሮ ንግስት ተወልድ ዳላስ።
ሻምበል አሸብር ገብሬ ዋሽንግተን ዲሲ።
ዶክተር ማ ት ዋሽንግተን ዲሲ
ሻምበል ሰለሞን ጋዲሳ ዳላስ ቴክሳስ።
ድል ያደርጋል;;
አቶ እዝራ በለጠ ላስ ቬጋስ ነቫዳ።
ውዴ አድገህ ዳላስ ቴክሳስ።
ሃይሌ ካሳ ሲዊስ።
ደምመላሽ ግርማ ስዊስ።
ጌታቸው እረዳ ሳንሆዜ ካሊፎርኒያ።


የውጪ ጋዜጠኞች ኮሚቲ ስም ዝርዝር ይቀጥላል።

Friday, April 3, 2015

በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!

Posted by Yeharerwerk Gashaw


'እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ
የመን ባለ ስደተኛ ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!! የገንዘብ እርዳታ አንፈልግም
       በግሩም ተ/ሀይማኖት
    የመን ባለችበት ችግር ውስጥ ኢትየጦጵያዊያን እያዩ ያሉት ስቃይ አሁን ብሶ ነው ያለው፡፡ ባለፈው ሰኞ ሀረድ የተባለ ቦታ መዝረቅ የተባለ የስደተኞች  ካምፕ የአየር ጥቃት ደርሶበት 46 ሰው ሞተ ብዬ ጽፌያለሁ፡፡ ይህን በተመለከተ አንድ አነስተኛና ጥቃቅን ስድብ አምራች የቻለውን ያህል ለመሳደብ ሞክሯል፡፡ እውነታው ግን  ያስጨነቃቸውም፣ እንዲሳደቡ ያደረጋቸውም በተለያየ ቦታ በስደተኛው ስም  ገንዘብ ለመሰብሰብ ቋምጠው የነበሩ ናቸው፡፡ በተለያየ ሚዲያ የመን ላለ ስደተኛ አሁን የሚያስፈልገው ህይወቱን የሚያድንበት መፍትሄ እንጂ ገንዘብ አለመሆኑን ደጋግሜ በመናገሬ መንገዱ ስለተዘጋባቸው ነው፡፡  አሁንም ደግሜ ደግሜ የምገልጸው የመን ያለ ስደተኛ ሀገሪቷ በአየር ድብደባ እየተደረገባት በመሆኑ ስደተኛው ላይ ሊደርስ የሚችለውን አስቦ የህይወት ማዳን ተግባር ከወገኖቹ ይጠብቃል እና ኢትዮጵያዊ ነን ያላችሁ በጦርነት መካከል UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ታደጉት ነው ጥሪዮ፡፡ በተለያየ መገናኛ ብዙሀን እንደተናገርኩት አሁንም እደግመዋለሁ UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ነፍስ ታደጉት፡፡ ለጊዜው የመን ያለ ስደተኛ የገንዘብ የምግብ ወይም መሰል ችግር አልገጠመውም እና ገንዘብ አሰባስቡ ለሚሏችሁ ገንዘባችሁን እንዳታወጡ፡፡ ለበላተኛ እንዳትሰጡ፡፡ ችግር ሲኖር ወቅቱን ጠብቆ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ ስለዚህ ጥቅማቸው የተነካ ሰዎች ሲሳደቡ ተቆጭታችሁ መልስ አትስጡ ያጣ ለማኝ ይሳደባል ነው ነገሩ፡፡ እንዲያውም እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ፡፡ በእኔ በኩል ግን ያለኝ መልስ ‹‹..ውሻ ጮኸ ብሎ የሚጮህ ቢኖር ውሻ ነው…›› የሚል ነው፡፡ እባካችሁ ለችግር ጊዜ ከተማራችሁት ስድብ ደጋግሙኝ….በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!'



20 hrs · 
፡ አሁንም ደግሜ ደግሜ የምገልጸው የመን ያለ ስደተኛ ሀገሪቷ በአየር ድብደባ እየተደረገባት በመሆኑ ስደተኛው ላይ ሊደርስ የሚችለውን አስቦ የህይወት ማዳን ተግባር ከወገኖቹ ይጠብቃል እና ኢትዮጵያዊ ነን ያላችሁ በጦርነት መካከል UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ታደጉት ነው ጥሪዮ፡፡ በተለያየ መገናኛ ብዙሀን እንደተናገርኩት አሁንም እደግመዋለሁ UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ነፍስ ታደጉት፡፡ ለጊዜው የመን ያለ ስደተኛ የገንዘብ የምግብ ወይም መሰል ችግር አልገጠመውም እና ገንዘብ አሰባስቡ ለሚሏችሁ ገንዘባችሁን እንዳታወጡ፡፡ ለበላተኛ እንዳትሰጡ፡፡ ችግር ሲኖር ወቅቱን ጠብቆ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ ስለዚህ ጥቅማቸው የተነካ ሰዎች ሲሳደቡ ተቆጭታችሁ መልስ አትስጡ ያጣ ለማኝ ይሳደባል ነው ነገሩ፡፡ እንዲያውም እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ፡፡ በእኔ በኩል ግን ያለኝ መልስ ‹‹..ውሻ ጮኸ ብሎ የሚጮህ ቢኖር ውሻ ነው…›› የሚል ነው፡፡ እባካችሁ ለችግር ጊዜ ከተማራችሁት ስድብ ደጋግሙኝ….በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!

ግሩም ተክለሃይማኖት የኢትዮጵያ ስዴተኞች በየመን እና ኢትዮጵያውያን በአረብ አገር ኮሚቲ ሊቀመንበር ሳና የመን።
Like · Comment · 

Ethiopian Refugees In Yemen Appoint Actress & Human Rights Activist Yeharerwerk Gashaw As International Representative.


Ethiopian Refugees In Yemen
‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ ግሩፕ›› 

መስራችና የየመን ስደተኞች ኮሚቴ
ግሩም ተ/ሀይማኖት::
ግልጽ መግለጫ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ
ጉዳዩ፡- የመን ያሉ ኢትዮጵያዊን ስደተኞች ችግር
በአረቡ አለም ላይ የተነሳውን አብዮት ተከትሎ የመን እስካሁን በጦርነት ስትማቅቅ 
ስደተኛውም ሲማቅቅ ከርሟል፡፡ከ2011 ጀምሮ ሞቅ በረድ የሚለው የእርስ በእርስ ጦርነት ስደተኛውንም ሲያሞቅ ሲያቃጥለው እዚህ ደርሷል፡፡ አሁን ተቃዋሚው የሁቲይ አማጺ ሚሊሻ ከፊል ሀገሪቱን ተቆጣጥሮ ሳለ በሳዑዲ አረቢያ አስተባባሪነት ስምንት ሀገሮች ካለፈው ሀሙስ 26/3/15 ጀምሮ የአየር ጥቃት እየሰነዘሩ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዜጎቼን ወደ ሀገሬ አስገባለሁ ብሎ መመዝገብ ጀምሯል፡፡ ወደ ሀገር መግባት የማይችሉ የፖለቲካና የተለያየ ችግር ያለባቸው በUNHCR ስር የስደተኛነት ማረጋገጫ ወረቀት (Mandate) ይዘው ያሉት ግን በጭንቅ ውስጥ ናቸው፡፡ መጨረሻዬ ምን ይሆን? በሰው ሀገር የሚለው ጥያቄ መልስ አልባ ሆኖባቸዋል፡፡ 

ጭንቅ ውስጥ ያስገባቸው የUNHCR ቢሮ ስደተኛውን ምንም ሳያደርግለት በትኖ ቢሮውን ዘግቶ በመውጣቱ ነው፡፡ 4000 ኢትዮያዊያን እና 1000 ኤርትራዊያን ስደተኞችን ምንም አይነት ከለላ ሳይሰጥ ሰራተኞቹን ብቻ ይዞ በመውጣቱ ስደተኛው ተስፋ ቆርጦ ሞቱን መጠባበቅ እጣ ፋንታው ሆነ፡፡ አሁን በየመን ይህን መሰል ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ይግጠም እንጂ በመላው አረብ ሀገራት ኢትዮጵያዊያን በስቃይ እና ተረግጠው፣ ተገፍተው ነው የሚኖሩት፡፡ ይህ በመሆኑ ችግራቸውን የሚፈታላቸው ጥቃት ሲደርስባቸው፣ ሲጎዱ ሲታመሙ የተለያየ ችግር ሲገጥማቸው አይዟችሁ የሚል ወገንም መንግስትም የላቸውም፡፡ ለምን ይሄ ተደረገባቸው? ለምን መብታቸው ተጣሰ? የሚል ባለመኖሩ የማንም መጫወቻ በመሆናቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያን ራሳቸው ያጠፋሉ፡፡ ታመው ወድቀው በዛው ይቀራሉ፡፡ በየሆስፒታሉ ሬሳቸው መጫወቻ እየሆነ ፍሪጅ ውስጥ ይቀራል፡፡ ታመው አስታማሚ በማጣት ችግሩ ይከፋባቸዋል፡፡ 

በፈርጅ ብዙ ችግር የታጠረው ኢትዮጵያዊ ስደተኛን ማንም ዞር ብሎ የሚያየው እኔ አለሁህ የሚለው ታጣ፡፡ በአረብ ሀገራት ያሉትን ስደተኞች ችግር በአምስት አመት በላይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል ወገኖቻችን እንዲሰሙ አደረኩኝ፡፡ ለወገን ተቆርቋሪ ነን ኢትዮጵያን እንወዳታለን የሚሉትን ሁሉ ‹‹ጎበዝ ወገን ረገፈ፣ ወገን ባህር በላው፣ወገኖቻችን ኤጀንሲዎች በዘመናዊ ባርነት ሸጧቸው፣ ኤምባሲውም ረሳቸው…ያላልኩት የለም፡፡ ለካ ኢትዮጵያን እንወዳታለን የሚለው ሁላ ኢትዮጵያን አፈርና ድንጋዩን ብቻ ነው የሚወዱት ህዝቡን አይፈልጉትም እስክል ድረስ በዝምታቸው ውስጥ ሰመጡ፡፡ 

ድረ-ገጾችም (ዌብ ፔጆችም) እነሱ በሚነፍሱበት አቅጣጫ የሚያራግብ መልዕክት ካልሆነ ስለስደተኛው አጀንዳቸው አይደለምና ገጻቸው ላይ መለጠፉን አይፈቅዱም፡፡ ሰሚ ጠፋ፡፡ ያለኝ አማራጭ አንድና አንድ ሆነና ‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊ ስደተኞችን መብት ጥሰት ድምጽ እናሰማ›› የሚል ላይክ ገጽ ከፈትኩ፡፡ በዛ ገጽ እና በዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ያሰባሰብኳቸውን ልጆች በማስተባበር ‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ ግሩፕ›› በዋትስአፕ አቋቋምኩኝ፡፡ በዚህ ግሩፕ ስር የበርካታ ልጆችን ችግር መፍታት ቻልን፡፡ ባለፈው ሀሙስ የመን ላይ የተጀመረውን የአየር ጥቃት ተከትሎ UNHCR ቢሮውን ጭርሱኑ ዘግቶ ሲወጣ እዚሁ ግሩፕ ላይ ተወያየንበት፡፡ ለመፍትሄ ያቀረብነው ሀሳብም የመን ካሉት ስደተኞች ውስጥ መሰባሰብ የሚችሉትን አሰባስቦ ኮሚቴ በማዋቀር ከውጭ ሊንቀሳቀሱልን የሚችሉ እንደ ከዚህ ቀደሙ አለን አለን ብለው መረጃችንን ወስደው መነገጃ የማያደርጉን ሰዎች መፈለግ እንዳለብን ወሰንን፡፡ ይህን ውሳኔ ተከትሎ እኔም በነጻ ፕሬስ ውስጥ ለሀገሬ የመናገር ነጻነት የታገልኩትን ረስተው የሚቶፍዝልኝ አጥቼ የመን መክረሜን አስመልክቼ ‹‹ግሩምዬ ያንተስ መጨረሻ ምንድን ነው?›› የሚል ርዕስ ሰጥቼ መረር ያለ መጣጥፍ ፌስቡክ ገጼ ላይ ለጠፍኩ፡፡

ወዲያው የሀረርወርቅ ጋሻው ምላሽ ሰጠችኝ፡፡ የቀድሞ ባህር ሀይሎች እና ከጅቡቲ አየር ሀይሎችን ወደ ሶስተኛ ሀገር ለማሻገር ያደረገችውን ትግል ሰምቼ ነበር፡፡ ከተወሰኑ የቀድሞ ባህር ኃይል እና አየር ሀይል ባልደረባዎች ጋር ተነጋገርኩ፡፡ ያንኑ ሀሳብ ‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ የዋትስአፕ ግሩፕ ላይ እና ለተሰባሰብነው የየመን ስደተኛዎች ኮሚቴ አቀረብኩ፡፡ ከየሀረርወርቅ ጋሻው ጋር ባለን ግንኙነት ላይ ተስማማን ወከልናትም፡፡ ሌሎችም ወገኖቻችን በየመን የከፋ አደጋ እንዳያጋጥማቸው ያላችሁ በጋራ ሰርታችሁ ካለንበት ህይወትና ሞት አጣብቂኝ ውስጥ እንድንወጣ ብታደርጉ ኢትዮጵያ ከእናንተ የምትፈልገውን ፍቅር መስጠታችሁ ብቻ ሳይሆን የአእምሮም፣ የህሊናም እርካታ ይሆናችኋል፡፡
‹‹በአረብ ሀገራት የኢትዮጵያዊንን ችግር መወያያ እና መፍትሄ መፈለጊያ ግሩፕ›› መስራችና የየመን ስደተኞች ኮሚቴ
ግሩም ተ/ሀይማኖት::

የመን በሚገኘው ስዴተኛ ስም ገንዘብ ከማንኛውም አገር ከተማ ውይም ቦታ ብትጠየቁ ገንዘብ እንዳትሰጡ እናሳስባለን።

የመን ያለው የኢትዮጵያ ስደተኞች በውጪ ጉዳይ አስፈጻሚ እና አለም አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቲ።

ዳላስ ቴክሳስ ዩኤስ ኤ።
April 3፡ 20015 በአሜሪካን አቆጣጠር።

ይድረስ መልክታችን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ።

የመን በሚገኘው ስዴተኛ ስም ገንዘብ ከማንኛውም አገር ከተማ ውይም ቦታ ብትጠየቁ ገንዘብ እንዳትሰጡ እናሳስባለን። ገንዘቡ በቀጥታ ለስዴተኛው የሚደርስበት የራሱ ኮሚቲ አቁዋቁሞዋል። በውጪም ከየመን የሚወጣበትን መንገድ እና ለመብቱ የሚታገሉለትን ወይዘሮ የሐረርወርቅን ጋሻውን ወክልዋል። ወይዘሮ የሀረወርቅ ጋሻው ለኢትዮጵያ ስዴተኞች መብት ያልተቁዋረጠ መታገል ሲያደርጉ ብቸኛዋ ናቸው። ስዴተኛው ወደ አሜርካን ካናዳ ሲውዘርላንድ፡ ፈረንሳይ ፡ እንግሊዝ አገር እና በሙርከኝነት በኤርትራ እስር ቤት ከነበሩት መለዮለባሹችንም ጭምር ወደ አውስትራልያ እንዲገቡ ያደረጉ ላለፈው 33 አመት ምሉ ያለምንም የግል ጥቅም ፡ ከማንም የገንዘብ እርዳታ ሳይደረግላቸው በስራቸው ያገኙትን እውቅና መድርክ በመጠቀም ለስዴተኛው ወገናቸው ከ18 አመት እድሜያቸው ጀምረው በፓሪስ ፍራንስ እስከዛሬም ሳያቁዋርጡ ድምጽ እና ተሙዋጋቹ ሆነው በማገልገል ይታወቃሉ። ሌላው አስተዋጽቆቸው በአረብ አገር በባርነት ሲኖሩ የነበሩትን ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለተባበሩት መንግስታት እና ለአለም መንግስታት በማቅረብ  በባርነት ቀንበር ተይዘው መንግስት የሚሙዋገትላቸው የሌላቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸው እንዳሉ እና ፓስፓርታቸው እየተቀማ በስቅላት ሳይቀር በአረቦች ሲደርስባቸው ለነበረው የባርነት ቀንበር ግፍ እንዲጋለጥ እና ሰዎቹም ነጻነታቸውን እንዲያገኙ ባደረጉትም የማይረሳ ለወገን ደራችነት ይታወቃሉ። ስዴተናው የኢትዮጵያ ስዴተኞች እናትም አባትም በሚል ስም ይጠራቸዋል። በቅርብም ከወጣቱ ትውልድ በሚል ስዴተኞች በስዊስ የሚገኙት በፌስቡክ ፔጅ በምስጋና ሸልመዋቸዋል። ዛሬም ቀጥለውበት በየመን የሚገኘውውን 5000 የኢትዮጵያ  ስዴተኛ 1000 ኤርትራውያን እና 19 በየመን የተረሱትን የቀድሞው የባሕር ሃይል ባልደረቦች ጉዳይ እንዲያስፈጽሙ ስዴተናው በውጪ ወኪላቸው አድጎዋቸዋል። ለዚሁም ከዚህ በታች ያለውን መግለጫ ይመልከቱ።

ገንዘቡ ሲያስፈልግ በቅርብ በየመን መረጋጋት እንደመጣ በሶስተኛ እጅ በስመአበሎ ሳይሆን በቀጥታ ከሕብረተስቡ ከአለም ዙርያ የመን ላለው ለስዴተኛው ኮሚቲ ለባለጉዳዩ ገንዘቡ የሚላክበት የተለመደው ለምሳሌ ከአሜሪካን እንድ እዌስተርን ዩንየን እና መኒግራንት ብሎም ከባንክ ወደ ባንክ ስራውን እስኪጀምር ድረስ በስዴተኛው ስም ገንዘብ አዋጡ ብሎ የሚጠይቃችሁ ብቅ ቢል ትናንትና እና ዛሬ እያደረጉ እንዳሉት በፌስቡክክም ዳርዳር እንደሚሉት በመልክተኞች እና እራሳቸው ሌላ ሰው ደጋፊዎቻቸው እያስመስሉ ስለሚመጡ እንዳትሞኙ፡ ገንዘባችሁን ጠበቅ አድርጋችሁ አስቀምጡ ለስዴተኛው እና ለልጆቹ እንላለን።

ከአክብሮት ጋር
ለማ ክብረት
ሕዝብ ግንኙነት።

ማንኛውም ድርጅት ነኝ የሚል የፓለቲካ ፓርቲነኝ ወይም አባል እና ደጋፊነን ፡ ሚዲያነን በሚል ቢቀርቡዋችሁ ገንዘባችሁን እንዳትሰጡ እናሳስባለን።

የመን ያለው የኢትዮጵያ ስደተኞች በውጪ ጉዳይ አስፈጻሚ እና አለም አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቲ።

ጥብቅ መግለጫ እና ማሳሰቢያ፡
April 1, 2015

የመን የሚገኙትን 5000ሺ ቀደም ስንል እንደገለጽነው የኢትዮጵያ ስዴተኞች 1000 ትግሪኛ ተናጋሪ ኢዮጵያውያን ከኤርትራ የተሰደዱ ትናንትና ጨምረናቸዋል ጉዳዩ አሳሳቢ በመሆኑ እና ሁሉም ኢትዮጵያዊ በመሆኑ። ሕዝቡ በስዴቱ አለም አብሮ እየተጋገዘ ነው ያለ ኢትዮጵያ ኤርትራ እያለ አይደለም። በጥቅሉ 6000 ኢትዮጵያውያን ስዴተኞችን አስመልክቶ ገንዘብ ለመላክ በሚል  ወይም ቁሳቁስ መግዣ የሚንቀሳቀሱ በተለመደው እንደተነሱ እንድናውቅ ተደርጉዋል ሕዝቡን እናመሰግናለን። ለዚህም ይፋ ያደረግንው ሁለት መግለጫዎች አንድ ከየመን አንድ ከዳላስ ለሕብረተሰቡ በፌስቡክ እና በተለያዩ መገናኛዎች በመድረሳቸው የተለመደው አወዛግቦ ገንዘብ መሰብሰብ ቦታ እንዳይኖረው እያደረገ ነው። ገንዘብ የሚጠይቃችሁ ማንኛውም ድርጅት ነኝ የሚል የፓለቲካ ፓርቲነኝ ወይም አባል እና ደጋፊነን ፡ ሚዲያነን በሚል ቢቀርቡዋችሁ ገንዘባችሁን እንዳትሰጡ እናሳስባለን። በውጪ የመን ላለው የኢትዮጵያ ስዴተኛ ወይም አረብ አገር ገንዘብ የሚሰበስብ አንድም አካል ወይም ግለሰብም እንደሌለም እንገልጻለን። ይሄንን መግለጫ የሚያወጣው ኮሚቲ ሊቀመንበር ወይዘሮ የሐረርወርቅ ነድፈው ባቀረቡት መሰረት የመን ላለው ኮሚቲ እራሱ ኮሚቲው ብቻ ገንዘብ የሚጠይቀውም የሚሰበስበውም የሚቀበልውም እንዲሆን አድርገው በመሆኑ የሁለቱም ኮሚቲ በአንድነት መስራት አንዱ ስምምነት መሆኑ ነው። ማንም ሰው ወይም ድርጂት የኢትዮጵይዊም ይሁን ይውጪ አገር ሰው፡ በየመንም ይሁን ከየመን ውጪ በስዴተኛው ስም ገንዘብ ሲቀበል ወይም ሲሰበስብ ቢገኝ በሕግ ያለፈውን ሁሉ ገንዘብ በማስረጃ በማቅረብ ብሎም በምስክር ገንዘቡን የወሰዱትን እያንዳንዳቸውን እንደምናደርግ እንደሚጠየቁበት እናሳስባለን። ድንገት የድርጅታቸው አባል በመሆናችሁ አዋጡ ቢልዋችሁ እና ብታስረክቡ ገንዘባችሁን እኛን ወይም የመን ያለውን ኮሚቲ የሚመለከት እንደማይሆን ከወዲሁ በግልጽ እዚህ ላይ እናስቀምጣለን። የመን ያለውን ሰዴተኛ ለመርዳት የሚፈልግ ሁሉ በግልጽ በምን መንገድ መርዳት እንደሚፈልግ ችሎታውን ማለት አቅሙን ፡ እና ከዚህ ቀደም በተግባር ለስዴተኞች ያደረገውን ሁሉ በፊለፍት ጠይቀን አቅርቦ የሚለው ወይም የምትለው በማስረጃ ከተገኘ እና ከዚህ በፊት በሕዝብ ስም በስዴተናው ምንም አይነት ጥቅም ያላካበተ ወይም ያልወሰደ መሆን እንዳለበት ከወዲሁ እናስታውቃለን። ዝምብሎ እረዳለሁ ብሎብቻ ስሙን በሚዲያ ካስታወቀ እና እራሱን እና ድርጅቱን አንጸባርቆ በመጨረሻም እጄን አንስቻለሁ የሚለውን ወይም የሱን አይነት አንቀበልም መክኒያቱም ሰው ባጋጣሚ እንደ የመን አይነት ቦታ ስላለ ነብሱ መጫወቻ ስላልሆነ ወይም መቀለጃ መነገጃ፡ እራስን ማስተዋወቅያ። ግልጽ እና ሃቀና ኢዮጵያዊ ብቻ ነው ወገኑን ለመርዳት እንዲተባበር የሚያስፈልገው ይሄውም በኮሚቲያችን ስር።

ገንዘቡ ሲያስፈልግ በቅርብ በየመን መረጋጋት እንደመጣ በሶስተኛ እጅ በስመአበሎ ሳይሆን በቀጥታ ከሕብረተስቡ ከአለም ዙርያ የመን ላለው ለስዴተኛው ኮሚቲ ለባለጉዳዩ ገንዘቡ የሚላክበት የተለመደው ለምሳሌ ከአሜሪካን እንድ እዌስተርን ዩንየን እና መኒግራንት ብሎም ከባንክ ወደ ባንክ ስራውን እስኪጀምር ድረስ በስዴተኛው ስም ገንዘብ አዋጡ ብሎ የሚጠይቃችሁ ብቅ ቢል ትናንትና እና ዛሬ እያደረጉ እንዳሉት በፌስቡክክም ዳርዳር እንደሚሉት በመልክተኞች እና እራሳቸው ሌላ ሰው ደጋፊዎቻቸው እያስመስሉ ስለሚመጡ እንዳትሞኙ፡ ገንዘባችሁን ጠበቅ አድርጋችሁ አስቀምጡ ለስዴተኛው እና ለልጆቹ እንላለን።

ከአክብሮት ጋር
ለማ ክብረት
ሕዝብ ግንኙነት።

Press Release Dallas Texas U.S.A
by Yeharerwerk Gashaw
Ethiopian Refugees' In Yemen Advocate Group USA
ግልጽ መግለጫ።
ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለስዴተኛው ከልብ ለተቁውርቁዋሪው።
በአሜሪካን አቆጣጠር ማርች 29፡ 2015
Dallas, Texas USA
ከወዲሁ ይቅርታ እጠይቃለሁ ከድካም እና በተለይ በተለያየ ቦታው ያለውን ኢትዮጵያዊ ስዴተኛ ጉዳይ የምሰራው ብዙ በመሆኑ አንዳንዴ ሲበዛብኝ በምጽፍበት ጊዜ ቃላቶች ሊዛነፉ እና ፊደሎት ሊጉድሉም ስለሚችሉ የማቶክረው መልክቱ ላይ እና ዋናው ቁምነገሩ ላይ እንጂ ቃላቶችን ማሳማር ላይ ስላለሆነ ስህተት ካያችሁ ከወዲሁ ይቅርታ እጠይቃለሁ። የማደርገው ሁሉ መተባበር ለገንዘብ ወይም ለግልጥቅም እንዳልሆነ እና ምንም አይነት የግልጥቅም ከድካም በስተቀር እንደማላገኝ ነገር ግን አምላክን እና ኢትዮጵያን አገልጋይ ብቻ መሆኔን በግልጽ ላስቀምጥ እወዳለሁ። ጊዜው ለወገን ቀኝ እጅ መሆን ምንጥቅም ቢኖረው ነው ወይም ጥቅም ስለሚገንበት ነው የሚል አባባል የተለመደ ሆንዋል ። መክኒያቱም ለጥቅም ስዴተውንም የአገሪቱንም ጉዳይ መነገጃ መኖሪያቸው ብዙዎቹ ስላደረጉት አልፎ አልፎ ደግሞ የዛሬ መቶ አመት እንደነበሩት አይነት ኢትዮጵያውያን ብንኖርም ልቆ የሚታየው አጭበርባሪው በመብዛቱ በመሆኑ። ሃቁን በማስቀመጥ አምናለሁ።
ይሄ ኢትዮጵያን ሪፊጂስ ኢን የመን አድቮኬት ግሩፕ ዩ ኤስ ኤ የጀመርኩት።
በአመሪካን አቆጣጠር ማርች 30፡ 2004 ከየመን የነበሩትን ስዴተኞች ባሕር ሃይሉን እና ሲቪሉን ወደ አሜኢርካን ለማስገባት ጉዳይ የሚያስፈጽም ኮሚቲ በማስፈለጉ የተቁዋቁዋመ ነበር። ከዚህም በታች የምንገልጸውን ጉዳይ አስመልክቶ በወጪ የሚደረገውን የስዴተኛውን ጉዳይ ማስፈጸም አስመልክቶ በዚሁ በአሜኢርካን ፡ በጄኔቫ በየመን በሰራው ስም የሚከናውን ይሆናል።
ከላይ ያለው ግሩፕ እንዴት እና ለምን እንዲቁዋቁዋም በጊዜው አስፈለገ አሁን ከዚህ በታች የማስቀመጠው ኮሚቲ አስፈላጊነት እና ጥቅሙ ባለጉዳዮቹን የራሳቸው ጉዳይ ተከታታይ የማድረጉ ጥቅም የጉዳያቸው ባለቤትንት አስፈላጊነቱን ሰሙኑን ጊዜ ሲፈቅድልኝ አስረዳለሁ።
የዚህ መግለጫ ዋና አላማ በየመን የሚገኙት ወገኖቻችን የኢትዮጵያ ስዴተኞች ካሉበት ከየመን ወደ አራት አገሮች የመሄድ ዘላቂ እድል እንዲኖራቸው ለማድረግ በየመን 4000 ስዴተኞችን ጉዳይ ለማስፈጽም ፡ የመንን በአሁን ጊዜ አስመልክቶ አምላክ የተመሰገነ ይሁን በስዴተኝነቱ እሳት ቀልጠው በፈተናው በመከራው ከተፈተኑት መሃል ወንድማችን አቶ ግሩም ተክለሃይማኖት ይገኝበታል። እሱም ቀደም ሲል ያቁዋቁዋመው ኮሚቲ የመን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ ስዴተኞች ባለቡት የመካከለኛው ምስራቅ ውስጥ ቅርንጫፍ ኮሚቲ እንዳለው ልረዳ ችያለው። ስለሆነም የተረሱትን 19 የቀድሞ ባህር ሃይል ባልደረቦች ጉዳይም በ4000 የስዴተኞች ጉዳይ ውስጥ በማጣመር በአንድ መሃከለኛ ኮሚቲ ስር ተባብረን አብረን ልንሰራ በእኔም በባህር ሃይሉ ባልደረቦች ከሲቪሎቹም ከአቶ ግሩምም ጋር በመነጋገር ተስማመተን ትግሉን ወይም ስራውን መጀመራችንን እገልጻለሁ።
በዚህ አጋጣሚ መግለጽ የምፈልገው የቀድሞው የኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች ዓለም አቀፍ ማህበር የመን ያለውን መለዮለባሽ አስመልክቶ የሚያስፈልጉ እርዳታዎች ስለሚጠበቀበት መረጃዎችን አስመልክቶ እስፓንሰርም የሚጠይቀውን ለማሙዋልት ይረዳ ዘንድ እንደሚተባበር ሙሉ ቃል ገብትዋል። ይሄ ማህበር ዋና ዓላማው የተጣመመውን የቀድሞውን ጦር ሃይሎች ታሪክ በሃቁ ለመጪው ትውልድ ተጽፎ እንዲተላለፍ እና ሌላው በእየአገሩ በስዴተኝነት እስካሁንም እየተንከራተተ ያለውን መለዮለባሽ የባህር ሃይሉን ጭምር ወደ ተሻለ አገር እንዲገባ የሚሰራ ሲሆን ይሄንን ክፍል እንድመራ በአምባሳደርነትም ድርጅቱና መለዮለባሹ ስለጣለብኝ የዜግነት ግዴታ እና እምነት በጣም አመሰግናለሁ። ይሄ ማሕበር ሲቁዋቁዋም በቀደሞው የኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች ስም የመጀመሪያው ሕግ ተመዝግቦ ትልቅ ሚና እያደረገ ያለ ብቸኛው ማሕበር ነው በ25 አገሮች እውቅና በዛሬ ጊዜ ተሰጥቶት ጉዳይ እያስፈጸመ ያለ። በበለጠ ለመረዳት ዌብ ሳይት ተመልከቱ።
ቀጥሎም የቀደሞው የኢትዮጵያ ባህር ሃይል አሶሴሽን በሚል የሚታወቀው አባላቶቹ የመን ላሉት ለ19 የባህር ሃይል ባልደረቦች እስፓንሰር እስከመሆን ድረስ እንደሚተባበሩ ሃሳብ አቀርበዋል በእኔ በኩል እነሱንም በጣም አመሰግናለሁ በዚህ አጋጣሚ።
ከየመን ከመጡት ውስጥም በላስ ቪጋስ በኩል ያሉት ሙሉትብብር እንደሚያደርጉ በትናንትናው እለት አስታውቀውኛል።
በመጨረሻም የስዴተኛው ጉዳይ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚመለከት ስለሆነ ፡ በየጊዜው ወንድማችን አቶ ግሩም ሲያቀርብ በነበረው ያልተነካ አልነበረም ካነበብኩት ስለሆነም እቀጥታ እያንዳንዳችሁ በዚህ ጉዳይ ገብታችሁ ከባለጉዳዮቹ ጋር ከአቶ ግሩም ጋር በመነጋገር የምትሰሩት ወይም የምታደርጉት አስተዋጽዎ ይኖራል። በመሆኑም ለወገን በመድረሳችሁ ያለሶስተኛ እጅ ወይም ሁለተኛ እኔንም የማይጨምር ማለት የምታደርጉት እርዳታ ለዝለአለም የሚያስደስታችሁ እና ምናልባትም በህይወታቸው የመጀመሪያው ስለሚሆን ስሜቱን በገንዘብ የማይገኝ ደስታውን ምንያህል ከውስጣችሁ እንደሚያለመልማችሁ ትገነዘባላችሁ። ለሁሉም አምላክ እንደሚረዳን እተማመንበታለሁ።
ከየመን ከስዴተናው ኮሚቲ እራሳቸውም መግለጫ ስለሚያወጡ በቀጥታ እንዴት እንደምታገኙዋቸው ይሰልክም ይሁን የኢሜል አድራሻ ታገኛላችሁ። ወንድም ግሩም ተክለሃይማኒትን፡ ወንድም መስፍን ባዩን፡ ወንድ ልኡልሰገድ አውጋቸውን ወንድም ጥላሁን እና ሌሎቹንም ጥይት በጆራችሁ ላይ እየተርዋርጠ የኤርፕሌን ድብደባው ወደ ሁዋላ ስታትሉ በቆራጥነት ሌት ተቀን ከእኔጋር በስልክ በመነጋገር መብራት በጠፋ ቁጥር ጭምር ያለባችሁን ስቃይ ስለተገነዘብኩኝ በእውነት የናንተ ጠንካራነት እኔን የበለጠ ስለጉዳያቸው ወገቤን አሰር አድርጌ የሚደርስብኝን ሁሉ ተቀብዬ በተለመደው እኔ ለጥሩ ስነሳ ተመሳሳይ ኮሚቲ እየፈጠሩ እኔ ለማዳከም የሚጥሩትን ትቼ ጉዳያችሁን ያለኝ አምላክ የሰጠኝን የአይምሮ ጠንካራነት ጉልበቴን በበለጠ እንድጠቀምበት እንዳነሳሳኝሁኝ እንድትውቁት እና ምስጋናም አቀርባለሁ ስለሁሉም በዚህ በሶስት ሳምንት ውስጥ ባሳለፍነው እናተ በየምን ምድር እኔ በአሜኢርካን ፕሌኖ ቴክሳስ ብሎም ዳላስ። በበኩሌ እዚህ ላይ አጠቃልዩ የሚቀጥለውን የስራውን ጅምር ይዤ እስካገኛችሁ ደህና እደሩልኝ መልካም የእሁድ ምሽት ይሁንላችሁ። ለዚህ መግለጫ ተጀምሮ መፈጸም እግዚአብሄርን አመሰግናለሁ።