Sunday, November 22, 2015

Stockholm Sweden : Ethiopian Andent Radio, Interview with W/O Yeharerwerk Gashaw

ካሳ ከበደ እና ግንቦት 7 (እሳት)በጠላት ሳንባ ነው የሚተነፍሱት:: የኢትዮጵያውነት መንፈስ የላቸውም::

ፕሮፌሰር መስፍንን ብቻ ነበሩ ሽንጣቸውን ይዘው ከዘራቸውንም ተመርኩዘው በኢትዮጵያዊነት ሳንባ ሲተነፍሱ የነበሩት።

የኢትዮጵያን ስም ለምን አነሱት? የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር የሚለው የግንቦት 7 አርበኞች ሆኑ ማለት ነው?
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያስብበት ይገባል። አሜሪካኖች ማወናበድ ሲያጋጥማቸው አስቡበት ይላሉ (think about it.)
ከዚህ ስር ያለውን አንብቡት ከግንቦት 7 ድህረ ገጽ  የተወሰደ ነው።
እኔ ከማንኛውም ግለሰብ ጋር ጸብ የለኝም በክርስትናዬ በሚመጣው እና በአገሬ ኢትዮጵያ እና ሕዝብዋን እንደሸቀጥ የሚሸጣት የሚቸረችራት የግለሰቦች መጥፎ ስራን እንጂ።

የኢትዮጵያወርቅ ጋሻው።

Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy (Ginbot 7) and Ethiopian People’s Patriotic Front (EPPF) merged. The united front will be called “Arbegnoch-Ginbot7 for Unity and Democracy Movement” (አርበኞች-ግንቦት7 የአንድነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ).



http://ethiopatriots.com/EthioAR/Ethiopia-Andnet-YEAHREWORK-GSHAW%20interview20151122-1700.mp3

Tuesday, November 17, 2015

የታሪክ አጋጣሚ እና የኢትዮጵያ አርበኞች ጀግኖች ትዝታዬ።

እንብዛም የማይነሱት እና የተረሱት የነጸነት አጎናጻፊዎቻችን ፡ ሃይለማሪያም ማሞ እና ፍቅረ ማሪያም አባተጫን።  ወያኔ እና ቀጣሪዎቹ የእነዚህን ንጀግኖች ብሄር ታሪክ ለመፋቅ : ለመቅበር ያልቆፈሩት የጀግንነት መቅበርያ መቃበር የለም መሬትዋ በጀግኖቹ ደም የምትኖር በመሆንዋ አልተቀበለቻቸውም እንጂ። አንዱ ምሳሌ የሃይለማሪያም ማሞ ሃኪም ቤት ነው አዳማ ሃኪም ቤት የተባለው። ይሄውም የደጃች ባልቻ አባነብሶን ሃኪም ቤት አዲስ አበባ ሃኪም ቤት ተብሎ እንደመጥራት ነው። የሁሉም ጀግኖች ታሪክ ከተቀመጠበት ፡ መነካት እና መቀስቀስ የለበትም ። በደማቸው በነብሳቸው ባጥንታቸው ላቆዩልን ነጻ አገር ሃውልት ፡ ሃኪም ቤት ማስታወሻ በዝቶባቸው ነው? የአንድነት ማስታወሻ ስለሆኑ? አንድነትን የሚጠላ ሁሉ የእጅ አዙር ነጋዴ ነጻ አውጪ እያለ በነጻነት እየኖረ ችግር መለወጥ ያልቻለ ነጻ አውጪ ነኝ እያለ ታሪክ ያጠፋል። ። ድል ለአንድ ኢትዮጵያ እና ለመላው ሕዝብዋ።

ይድረስ ለመላው ኢትዮጵያዊ አዲሱ ትወል ለሴቱም ለወንዱም።

በኢትዮጵያወርቅ ጋሻው (የሐረርወርቅ)

 ትልቅ የሰው ልጅ ሕግ እና ፍርድ ቤት፡ የሕይወት መመሪያ እግዚአብሄር ነው። ፈጣሪን አምኖ ሕጉን ተከትሎ መኖር የመጀመርያው እና ትልቁ የሰው ልጅ ሕይወት የደስታው ዋስትና እና ሙሉ የሰው ልጅ ሕይወት አንዋንዋር የመኖሩ ዋስታናውን በራሱ ሕሌና ተሸንፎ እራሱን አክብሮ ማስከበርን ለራሱ የማስተማር እና ማሳመን ግዴታውን መወጣትን ነው።

ሁለተኛው የሰው ልጅ የራሱን ታሪክ አክብሮ አስከብሮ ሌሎቹ ጥሩ ጥሩውን እንዳስረከቡት ሁሉ ለቀጣዩ ትውልድ በበለጠ ጥሩ ፡ ጥሩውን ጨምሮ ገንብቶ የማስረከብ የዜግነት ግዴታውን ሲወጣ ነው። አለበለዚያ ሙሉ የሰው ልጅ ሕይወት አለው ማለት አይቻልም ለአለም ሸክም ከመሆን ሌላ ። ሲሞትም እንደቆመባት ቦታ ሁሉ ሌላ ሸክም ሆኖ ምድርን አጣባቢ ይሆናል በመቃብሩ ማለት ነው።

ወጣቱ ትውልድ ዛሬ የማካፍልህ እራስህ አንብበህ ሃቁን ልትረዳው ከምትችለው የሃቅ የታሪክ ማሕደር ተቀንጭቦ ከተሰጠኝ ሲሆን ይሄውም ለአንተም ላንቺም ፡ ለእኔም ነጻነትን ስላጎናጸፉን ጀግኖቻችን ከብዙዎቹ በታሪካቸው በጀግንነታቸው የመጀመርያ የጦሩ መእራፍ እና የጦሩ ገበሬ ከነበሩት የመቶ አለቃ ሃይለማሪያም ማሞን እና የደጃዝማች ፍቅረማርያም አባተጫንን ጀግንነት እና ውለታ ነው። አስታውስ በብሄር፡ በትውልድ ሃረግ፡ በክልል ሳይሆን የተዋደቁት በአንድ አገር ፡ በአንድ ሕዝብ እና በአንድ ሰንደቅ አላማ ስም ለማሉላት እናት አገራቸው እና ወገናቸው፡ ስንደቅ አላማችን ለእኔ ላንተ ላንቺ ነጻነት እንደነበር።

ወያኔ በመእራባውያን እና አረቦች እየተረዳ ወደ ቤተመንግስት ከመግባቱ አንድ አመት በፊት የአርበኞች ማሕበር በጊዜው በሕይወት ተርፈው ሳይደላቸው ባጎንጸፈኡት ነጻነት ደልቶት ተርፎት ጭምር የሚኖር ተመልካች ሆነው እየተራቡ ሲኖሩ የነበሩት እና የረባ እንክዋን እንቅል ሳይተኙ እንደው በሃሳብ ነገ ምን እበላ ይሆን እያሉ አንዳንዱም ማደሪያ እንክዋን አጥቶ በዚህ መልክ የሚኖሩት ለአርበኞች ማሕበር ጽሕፈት ቤት ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ማሕበሩን እነዚህ ጀግኖች እያስጎበኙኝ እያስረዱኝ ፡ እያስተማሩኝ ጉብኝቴን እጨረሳለሁ በቀኑ። ከዛም ከመሰናበቴ በፊት በእጄ ጀግኖቹ እራሳቸው ፡ ሽልማት የጀግኖች ታሪክ ከዚህ በታች ጥቂቱን ከመሃሉ የማቀርበውን ሁለት ቲኒንሽ እንደ ደብተር የተጠረዘ የእያንዳንዱን ጀግና ታሪክ ያሰፈረውን የታሪክ ክብር ያወርሱኛል ይሄውም በጊዜው ሱማሊ እናም የወጽት ጠላት ሕዝቡን እና ሰራዊቱን በአራቱም ማእዘን ጦርነት ገጥመውት ስላደረኩት አገሬ ገብቼ ከሰራዊቱ ጎን በመሰለፍ ካስፈለገም ለጦርነቱም ሰልጥኝ የዜግነት ግዴታዬን ለመወጣት ዝግጁ ስለነበርኩኝ ወደ አሜሪካን ለመመለስም ምንም ፍላጎትም አልነበረኝም። ያም ነበር ጀግኖቹን ከእኔ ጋር ያገናኛቸው። ሌላው የአጼ ቴዎድሮስ ፡ የንግስት ጣይቱ እና የጀግኖች ታሪክ በሃውልት የማሰራቱ ሕልሜ ትልቅ ስለነበረ ማለትም ቲኒሽ ሆኜ የሰማእታት መቃብር እየተባለ በሳጥን ተከምሮ ስላሴ በአብድ ክፍት መቃብር ውስጥ ካየሁት ጀምሮ በ13 አመት እድሜዬ ሁሌም ምኞት ነበረኝ እና ይሄንንም ለፕሬስ በሰጠሁት መግለጫ ሲሰሙ አስታዋሽ አገኝን በሚል ከሌላ ሳይሆን ከራሳቸው ከጀግኖቹ በመጣ ደግነት ተመርቄ በጊዜው ከነበሩት የጀግኖች ማሕበር ሊቀመንበር ቀኛዝማች ኢብሳ የመሃበሩ መተዳደሪያ ደንብ ተፈርሞ ተሰጥቶኝ በሽልማት መልክ ተሰነባብቼ ከጽህፈት ቤቱ ሕንጻ እወጣለሁ። የማይረሳኝ ጀግኖቹ እውጪ ድረስ ወጥተው የልባቸውን ችግር ካካፈሉኝ በሁዋላ ስላላቸው ችግር ከሁሉም የጀግናውን ታሪክ ሃውልቱን ማሰራቱን በቶሎ እንዳደርገው አሳስበውኝ እንለያያለን።

ከሶስት ቀን በሁዋላ ስልክ ይደውልልኝ እና ወደ ጀግኖች ማሕበር ጽህፈት ቤት ተመልሼ እንደሄድ ይነገረኛል ። ጥሪያቸውን አክብሬ በቦታው እገኛለሁ። ጀግኖች "የኢትዮጵያወርቅ ጋሻው "የጥናታዊ ኢትዮጵያ የጀግኖች ማህበር አለም አቀፍ እንደራሴ" መደረጌን እና የዜግነት ግዴታየም በአደራ መልክ ጭምር ሁለት ተግባሮችን በስራ እንዳውል ይነገረኛል። እኔም በደስታ ከዛ ሁሉ የፋሽስት ጦርነት አገሬን ሕዝቡን ነጻ አውጥተው እኔም ያለእናት ያለአባት በነጻነቴ አገሬ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደልቤ ያለመንም ክልል መወሰን እንዳደግ ነጻነቴን ባጎናጸፉኝ ጀግኖች የተሰጠኝ ሃላፊነት በደስታ ተቀበልኩት። በተግባር ለመተርጎምም ቅድሚያዬ አድርጌው ነበር። ይሄም ጥንታዊ ኢትዮጵያ የጀግኖች አርበኞች ማሕበር እንደራሴ ብሎ ግለሰብ አገር ወዳድ ሲሰይም በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ በመሆኑ ትልቅ ሽግር ሳይፈጠረብኝ ያለፈ እንዳይመስላችሁ። ሆኖም አስብበት እና ጉዳይ አስፈላጊ ከመሰለኝ አካፍላችሁዋለሁ። ይቀጥላል።


















Monday, November 9, 2015

2015 Multi-choice Ethiopian Journalists and Programs Awards Nominees.

Honoring Outstanding Ethiopian Journalists International Committee U.S.A.Dallas, Texas  Legally registered and recognized In USA


Journalists, of the year 2015 in various categories 

Multi-choice Awards final Nominees are:
Worku Mola, Andenet Radio
Martha Tsegaw, SBS Radio 
Girum Teklehaimanot, a Free lance journalist, Reporting from Yemen War zone.
Tekola Worku, YeEthiopia Andenet Radio 

The Best Ethiopian International broadcasting Programs Award final Nominees are,  
1.Andenet Radio, Stockholm, Sweden.
2.http://ethiopatriots.com, Stockholm, Sweden.
3.Ethiopian Semay,  San Jose, California.

4. SBS Amharic Program, Australia.

 Our goal is to motivate journalists and educate the public in the importance of transparent journalism within the Ethiopian society.

Journalist Kassahun Seboqa, was the fist  recipient of our organization's award in 2014 "Man of the Year 2014"  



SBS congratulates Kassahun Seboqa on receiving "Man of the Year 2014" and the SBS Amharic Radio program as "Best International Ethiopian Radio Program" award. Kassa honored by Ethiopian Unity People's Voice Congress, DFW Ethiopian Community & Ethiopian Women for Peace and Democracy, DFW Ethiopian Community Blog, and Honoring Outstanding Ethiopian Journalists International Committee USA.

(Image - Gonzalo Lopez (L) Program Manager and Kassahun Seboqa (R) Executive Producer of the SBS Amharic Program - Photo by Ibrahim Mohamed)

Like · Comment · Share
Comments
Temesgen Berhe I saw so many ethiopia journalist this man is my hero. congratulation kassa keep it up
SBS Amharic Many thanks, Temesgen.

Saturday, November 7, 2015

የተባበሩት ፡ መንግስታት፡ የተቁዋቁዋመበትን 70ኛ ፡ አመት በዳላስ ቴክሳስ ተከበረ።



በቦታው በመገኘት የተዘጋጀ ዘገባ።
በበቀለ ወዳጆ።
የኢትዮጵያ ስደተኞች ኮሚቲ አባል ዳላስ።

  የተባበሩት ፡ መንግስታት፡ ድርጅት ፡ ሰባኛ የምስረታው በአል ኖቬምበር 3፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣንና ተወካይ በተገኙበት በዳላስ ቴክሳስ በደመቀ ስንስርአት ተከብሮአል። የክብር እንግዳውና፡ ንግግር ያደረጉት ፡  ዶክተር ፡ ሰርጃን ፡ ከሪም ፡ ወደ ዳላስ እንደገቡ በተዘጋጀላቸው ልዩ ስፍራ የእንክዋን ደህና መጡ የክብር አቀባበል የአበባና አጭር ገለጻ በየሐረርወርቅ ጋሻው ተደርጎላቸዋል። በቅርብ የተባበሩት ፡ መንግስታት ፡ ዋና ጸሃፊ ፡ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁት ዶክተር ሰርጃን ከሪም በበአሉ ላይ አዳራሹን ለሞላው ሕዝብ ሲገልጹ ፡ የመነጋገሪያቸው ዋና ትኩረት አድርገው ያቀረቡት የሲሪያንና የኣፍሪካን ስዴተኞች አስመልክቶ ነበር። ኢትዮጵያ የተባበሩትን መንግስታት ከጥንሡ ካቁዋቁዋሙት አገሮች አንድዋ ነች።

ከዚህ በታች ፡ ያሉት ፎቶግራፎች ፡ የሚያሳዩት ፡ የሐረርወርቅ ጋሻው ፡  የተባበሩትን መንግስታት ድርጅትን ፡ ድህነትን ለማጥፋት ፡ የሚደረገውን ዘመቻ ፡ መፈክር ይዛ እንድትነሳ ፡ በተጠየቀችው መሰረት ፡ የምርጫዋን ይዛ ፡ የተነሳችውና ለዶክተር ካሪም የእንክዋን ደህና መጡ አቀባበል ፎቶግራፍ።   ፎቶ በማይክል ዌብስተር ዩኤን።

Below, Yeharerwerk Gashaw, Actress and International Human Rights Activist,
welcoming Dr. Kerim of UN.
 Pictures by Michael Webster UN








Saturday, July 4, 2015

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መንግስት : ከፕሬዘደንት ኦባማ ጋር በግልጽ ለመነጋገር ጥያቄ አቀረበ::


የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መንግስት
 (Ethiopian Natioanl Govenment In Exile)
Founded in Dallas Texas in 2008 Legally.

Dallas, Texas U.S.A
 July 3, 2015
ይፋ መግለጫ።

ከፕሬዘደንት ኦባማ ጋር በግልጽ ለመነጋገር:

      የኢትዮጵያ በሔራዊ የስዴት መንግስት ከፕሬዘደንት በራክ ኦባማና ከአምስት የአሜርካን መክር ቤት አባሎች ጋር የኢትዮጵያና ሕዝብዋን ወቅታዊ ጉዳይ ላይ በይፋ ለመነጋገር ባቀረበው የሃያ ደቂቃ ቀጠሮ ጥያቄ መሰረት መልሳቸውን እየተጠባበቀና እየተከታተለ መሆኑን ለጉዳዩ ባለቤት ለሆነው ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያስታውቃል።

      የስዴቱ መንግስት ለመነጋገር ካቀረባቸው የመነጋገርያ ነጥቦች መሃል አንደኛ፡ ስለ ፕሬዘደንት ባራክ ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ እቅዳቸውን እንዲሰርዙ። ሁለተኛ፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ተደረገ የተባለውን የዚህ ዓመት ምርጫ የሃሰት ምርጫ ከመሆኑ በተጨባጭ የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት ተወዳዳሪውም፡ አሸናፊዎችም 100% ለማሸነፉም አጽዳቂ በጠመንጃ በማስፈራራትና በመግደል ላይ የተፈጸመ በመሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መግንስት እንዳልተቀበለ።  ሶስተኛ፡  በግፍ በትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት ስለተገደሉት የተቃዋሚ ፓርትይ ተወዳዳሪዎች፡ አባላትና መሪዎች። አራተኛ፡ በእስር ላይ እየተሰቃዩ ስላሉት  ጋዜጠኞችና የፓለቲካ እስረኞች ይለቀቁ የሚል ጥያቄን ያካተተ አርስቶች ይገኙበታል።      
  
     እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መንግስት የአሜሪካን ሕግ በሚፈቅደው መሰረት በሕግ ተመዝግቦ በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2000 የምርጫ ዘጠና ሰባትን ድል ተቀዳጅቶ የነበረው የድሉ ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ በአገር ቤትም ይሁን በውጪ ያለው እንደተደሰተ ያህል ብዙም ሳይቆይ በማግስቱ ድሉን ሲቀማ በአገር ቤትም በውጪም የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሞራሉ ያልወደቀ ተስፋ ያልቆረጠ ሰው አልነበረም። በመሆኑም ለኢትዮጵያና ሕዝብዋ መብት የሚቆም አንድም ድርጅት የሚነቃነቅ በጊዜው በመጥፋቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ የድሉ ባለቤትነቱን መልሶ እንዲረከብ በማሰብ "የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መንግስት" በሚል ሕጋዊ እውቅና ያለው የስዴት መንግስት ማቁዋቁዋም ብቸኛውና ትክክለኛው አማራጭ ነበር።  በመሆኑም የስዴቱ መንግስት ብዙ አተዋጽዎ አድርግዋል እስከዛሬ። አሁንም ልክ እንደምርጫ ዘጠና ሰባት የሕዝቡ ሞራል ከመነካቱም ባሻገር በሃዘን ላይ ሃዘን  ስለተደራረበበት ልጆቹም በአይሰስ ፋሽስት ስለታረዱበት፡ በመትረየስም ስለተፈጁበት፡ በየመንም ስላለቁበት፡ መከራውን መሸከም አቅቶት የወገን ያለህ እያለ በሚገኝበት ጊዜ የለመደው የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት 2015 ምርጫ አሸናፊንኝ መቶ በመቶ አሸነፍኩ በሚል ሕዝቡና አገሪቱ ላይ ተፈናጦ ማን ያነቃንቀኛል በሚል የሕዝቡ ሃዘን ላይ ሌላ ከባድ ሃዘን አከናነበው። ታሪክ የጣለብን ሃላፊነት ነውና ግዴታ የኢትዮጵያንና የሕዝብዋን ችግር አንጋፋ ድርጅቶች ጥሪያችንን ተቀብለው በቅርብ የትግሉን ሜዳ በሕዝቡና በአዲሱ ትውልድ አድሰው ትግሉን እስኪጀምሩ ድረስ ሜዳላይ የአገርና የሕዝብ ጉዳይ ስለማይጣል ሃላፊነት ተረካቢው እስኪመጣ በቅርብ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መንግስት ስራውን በመቀጠል የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት በሚያደርገው በማንኛውም ስምምነትና ውሳኔ ላይ የኢትዮጵያን ሕዝብ የማይወክል መሆኑን ለአሜሪካንም ይሁን ለአለም መንግስታት ብሎም የንግድ ድርጅቶች ጭምር ውላቸው በሕዝቡ በኩል ቦታ እንደሌለው እናስታውቃለን ለአገሪቱና ለሕዝቡ እንቆማለን።

     በዚህ አጋጣሚ የአንጋፋ የኢትዮጵያ ፓለቲካ ድርጅቶች በስምምነት አንድ ወጥ የሆነ የፓለቲካ ድርጅት በማቁዋቁዋም ኢትዮጵያንና ሕዝብዋን ከትግራይ ነፃ አውጪና ከግብር አበሮቹ እጅ ነጻ እንዲያወጡት፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መንግስት አንጋፋዎቹን እያነጋገረ መሆኑን ይገልጣል።  የኢትዮጵያም ሕዝብ እነዚህ አንጋፋ ድርጅቶችና መሪዎቻቸውን በከፍተኛ የድረሱልን ጥሪ ጮሆ እየጠራቸው ይገኛል። እነሱም ሕዝቡን ሊያዳምጡትና ሊሰሙት ይገባል። አንጋፋ ድርጅቶች እንደሚታወቀው አራት ናቸው ሚኤሶን፡ ኢፒአርፕ፡ መድህንና የመላው ኢትዮጵያ።

     አንጋፋ ድርጅቶቹ እንደ ወርቅ አንባር ተጨፍልቀው አንድ ድርጅት ኢትዮጵያንና ሕዝብዋን ነፃ አውጪ ድርጅት እንዳቁዋቁዋሙ፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስዴት መንግስት ድርጅቱን አስረክቦ ባዶ ሜዳላይ ተጥሎ የነበረውን የኢትዮጵያንና የሕዝብዋን ጉዳይ ክብርና ሞራል ቀና በማድረግ የሰራውን ታሪክ ለወጣቱ ትውልድ እዲተላለፍና ለወደፊትም ትምህርት ይሆነው ዘንድ ለሚተካው ትውልድ በሕጋዊ መንገድ እንደሚያስረክብ ያስታውቃል።

 ኢትዮጵያና ሕዝብዋ አንድነታቸውንና ነጻነታቸውን አስከብረው ለዘለዓለም ይኖራሉ።
የኢትዮጵያወርቅ ጋሻው (የሐርርወርቅ)
መስራችና ሊቀመንበር።

For more information please, visit dfwethiopiancommunity.blogspot.com