Friday, June 5, 2015

የገንዘብ እርዳታ አንፈልግም! የኢትዮጵያ ስዴተኞ ።

June 5, 2015

ይድርስ ከኢትዮጵያ ስዴተኞች የመን እና ሊብያ በውጪ ለሚገኘው የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ።

ቀደም ስንል ከአንዴም ሁለቴ ገንዘብ ሳይሆን የምንፈልገው ተባብራችሁ ካለንበት የመከራ አጣብቂኝ እንድታድኑን ነው ማለታችን ይታወሳል። ሆኖም በዳላስ ቴክሳስና በአትላንታ በተለያዩ የአሜሪካን ከተሞች በስማችን $100 ዶላር በትኬት በመሸጥ ገንዘብ እየተሰበሰበ መሆኑን በማስረጃ ተረድተናል ይሄም በጣም አሳዝኖናል። የት እንዳለን እንክዋን ያልፈለጉን ያልጠየቁን እኛ ስላለንበት መከራና ስቃይ ያልተቀበሉት ያልደረሱልን ገንዘብ ሰብስበው ምን ልያደርጉት ነው? ግማሾቻችን በቦንብ ላሸቅን ከእነልጆቻችን፡ ገማሾቻችን ታረድን ባዳው እንክዋን ሲያዝንልን ይሄ እንክዋን እንዴት በውጪ በተለየም በአሜሪካን ያለው ውገናችን አይተባበርንም ? ገንዘብ ከዚህ ቀደም ከእየከተማው ከአሜሪካን ተዋጣ ሰማን እናንም ቃለመጠየቅ ተደረገል ሆኖም ገንዘቡን የተቀበሉት በስማችን  አንድም ሳንቲም ከሳውዲ ወደ የመን የገባው ጭምር አላገኘንትም።

የኢትዮጵያን ሕዝብ በአሜሪካንም ይሁን በመላው አለም የምትገኙትን ለስዴተኞች በመን፡ በሊብያ ባለውና በሳውዲ ለሚገኙት ኢትዮጵያውያን ወዘተ በሚል ስም ገንዘብ ለእኛ ለስዴተኞች አዋጡ ለሚልዋችሁ ሁሉ ለፓለቲካ ድርጅቶች፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ፡ የመረዳጃ ማሕበር፡ የሃይማኖት ድርጅቶችና ማንኛውም የውጪ ድርጅት ሳይቀር ገንዘብ በስማችን እንዳትሰጡ። መቼ እና እንዴት እንደምትልኩልን በእየ ድርጅቶቻችሁ እራሳችን ከየመንና ከሊብያ በጥምረት አሜሪካን ዳላስ ካለው የወከልነው ብቸኛው አማራጫችን በችግራችን ከተገኘለን ---ጋር በምናወጣው መግለጫ እናስታውቃለን።  እስከዛሬም የሰጣችሁትን መልሳችሁ እንድትቀበሉ ገንዘባችሁን እናሳስባለን።
ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ አሜሪካን ዳላስ መቀመጫው የሆነውን በውጪ ወኪላችንን
በ214-642-0394 ማናገር ይቻላል። ቀደም ሲል ያወጣናቸውን ከዚህ በታች ይመልከቱ።

የስዴተኞች ኮሚቲ
ከየመን።


'እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ
የመን ባለ ስደተኛ ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!! የገንዘብ እርዳታ አንፈልግም
       በግሩም ተ/ሀይማኖት
    የመን ባለችበት ችግር ውስጥ ኢትየጦጵያዊያን እያዩ ያሉት ስቃይ አሁን ብሶ ነው ያለው፡፡ ባለፈው ሰኞ ሀረድ የተባለ ቦታ መዝረቅ የተባለ የስደተኞች  ካምፕ የአየር ጥቃት ደርሶበት 46 ሰው ሞተ ብዬ ጽፌያለሁ፡፡ ይህን በተመለከተ አንድ አነስተኛና ጥቃቅን ስድብ አምራች የቻለውን ያህል ለመሳደብ ሞክሯል፡፡ እውነታው ግን  ያስጨነቃቸውም፣ እንዲሳደቡ ያደረጋቸውም በተለያየ ቦታ በስደተኛው ስም  ገንዘብ ለመሰብሰብ ቋምጠው የነበሩ ናቸው፡፡ በተለያየ ሚዲያ የመን ላለ ስደተኛ አሁን የሚያስፈልገው ህይወቱን የሚያድንበት መፍትሄ እንጂ ገንዘብ አለመሆኑን ደጋግሜ በመናገሬ መንገዱ ስለተዘጋባቸው ነው፡፡  አሁንም ደግሜ ደግሜ የምገልጸው የመን ያለ ስደተኛ ሀገሪቷ በአየር ድብደባ እየተደረገባት በመሆኑ ስደተኛው ላይ ሊደርስ የሚችለውን አስቦ የህይወት ማዳን ተግባር ከወገኖቹ ይጠብቃል እና ኢትዮጵያዊ ነን ያላችሁ በጦርነት መካከል UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ታደጉት ነው ጥሪዮ፡፡ በተለያየ መገናኛ ብዙሀን እንደተናገርኩት አሁንም እደግመዋለሁ UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ነፍስ ታደጉት፡፡ ለጊዜው የመን ያለ ስደተኛ የገንዘብ የምግብ ወይም መሰል ችግር አልገጠመውም እና ገንዘብ አሰባስቡ ለሚሏችሁ ገንዘባችሁን እንዳታወጡ፡፡ ለበላተኛ እንዳትሰጡ፡፡ ችግር ሲኖር ወቅቱን ጠብቆ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ ስለዚህ ጥቅማቸው የተነካ ሰዎች ሲሳደቡ ተቆጭታችሁ መልስ አትስጡ ያጣ ለማኝ ይሳደባል ነው ነገሩ፡፡ እንዲያውም እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ፡፡ በእኔ በኩል ግን ያለኝ መልስ ‹‹..ውሻ ጮኸ ብሎ የሚጮህ ቢኖር ውሻ ነው…›› የሚል ነው፡፡ እባካችሁ ለችግር ጊዜ ከተማራችሁት ስድብ ደጋግሙኝ….በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!'



20 hrs · 
፡ አሁንም ደግሜ ደግሜ የምገልጸው የመን ያለ ስደተኛ ሀገሪቷ በአየር ድብደባ እየተደረገባት በመሆኑ ስደተኛው ላይ ሊደርስ የሚችለውን አስቦ የህይወት ማዳን ተግባር ከወገኖቹ ይጠብቃል እና ኢትዮጵያዊ ነን ያላችሁ በጦርነት መካከል UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ታደጉት ነው ጥሪዮ፡፡ በተለያየ መገናኛ ብዙሀን እንደተናገርኩት አሁንም እደግመዋለሁ UNHCR ጥሎት የወጣውን ስደተኛ ነፍስ ታደጉት፡፡ ለጊዜው የመን ያለ ስደተኛ የገንዘብ የምግብ ወይም መሰል ችግር አልገጠመውም እና ገንዘብ አሰባስቡ ለሚሏችሁ ገንዘባችሁን እንዳታወጡ፡፡ ለበላተኛ እንዳትሰጡ፡፡ ችግር ሲኖር ወቅቱን ጠብቆ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ ስለዚህ ጥቅማቸው የተነካ ሰዎች ሲሳደቡ ተቆጭታችሁ መልስ አትስጡ ያጣ ለማኝ ይሳደባል ነው ነገሩ፡፡ እንዲያውም እባካችሁ የሚሰድቡኝን አድንቁልኝ፡፡ በእኔ በኩል ግን ያለኝ መልስ ‹‹..ውሻ ጮኸ ብሎ የሚጮህ ቢኖር ውሻ ነው…›› የሚል ነው፡፡ እባካችሁ ለችግር ጊዜ ከተማራችሁት ስድብ ደጋግሙኝ….በስደተኛው ስም ግን ገንዘብ አዋጡ ብሎ መብላት አይቻልም!!!

ግሩም ተክለሃይማኖት የኢትዮጵያ ስዴተኞች በየመን እና ኢትዮጵያውያን በአረብ አገር ኮሚቲ ሊቀመንበር ሳና የመን።