Tuesday, November 17, 2015

የታሪክ አጋጣሚ እና የኢትዮጵያ አርበኞች ጀግኖች ትዝታዬ።

እንብዛም የማይነሱት እና የተረሱት የነጸነት አጎናጻፊዎቻችን ፡ ሃይለማሪያም ማሞ እና ፍቅረ ማሪያም አባተጫን።  ወያኔ እና ቀጣሪዎቹ የእነዚህን ንጀግኖች ብሄር ታሪክ ለመፋቅ : ለመቅበር ያልቆፈሩት የጀግንነት መቅበርያ መቃበር የለም መሬትዋ በጀግኖቹ ደም የምትኖር በመሆንዋ አልተቀበለቻቸውም እንጂ። አንዱ ምሳሌ የሃይለማሪያም ማሞ ሃኪም ቤት ነው አዳማ ሃኪም ቤት የተባለው። ይሄውም የደጃች ባልቻ አባነብሶን ሃኪም ቤት አዲስ አበባ ሃኪም ቤት ተብሎ እንደመጥራት ነው። የሁሉም ጀግኖች ታሪክ ከተቀመጠበት ፡ መነካት እና መቀስቀስ የለበትም ። በደማቸው በነብሳቸው ባጥንታቸው ላቆዩልን ነጻ አገር ሃውልት ፡ ሃኪም ቤት ማስታወሻ በዝቶባቸው ነው? የአንድነት ማስታወሻ ስለሆኑ? አንድነትን የሚጠላ ሁሉ የእጅ አዙር ነጋዴ ነጻ አውጪ እያለ በነጻነት እየኖረ ችግር መለወጥ ያልቻለ ነጻ አውጪ ነኝ እያለ ታሪክ ያጠፋል። ። ድል ለአንድ ኢትዮጵያ እና ለመላው ሕዝብዋ።

ይድረስ ለመላው ኢትዮጵያዊ አዲሱ ትወል ለሴቱም ለወንዱም።

በኢትዮጵያወርቅ ጋሻው (የሐረርወርቅ)

 ትልቅ የሰው ልጅ ሕግ እና ፍርድ ቤት፡ የሕይወት መመሪያ እግዚአብሄር ነው። ፈጣሪን አምኖ ሕጉን ተከትሎ መኖር የመጀመርያው እና ትልቁ የሰው ልጅ ሕይወት የደስታው ዋስትና እና ሙሉ የሰው ልጅ ሕይወት አንዋንዋር የመኖሩ ዋስታናውን በራሱ ሕሌና ተሸንፎ እራሱን አክብሮ ማስከበርን ለራሱ የማስተማር እና ማሳመን ግዴታውን መወጣትን ነው።

ሁለተኛው የሰው ልጅ የራሱን ታሪክ አክብሮ አስከብሮ ሌሎቹ ጥሩ ጥሩውን እንዳስረከቡት ሁሉ ለቀጣዩ ትውልድ በበለጠ ጥሩ ፡ ጥሩውን ጨምሮ ገንብቶ የማስረከብ የዜግነት ግዴታውን ሲወጣ ነው። አለበለዚያ ሙሉ የሰው ልጅ ሕይወት አለው ማለት አይቻልም ለአለም ሸክም ከመሆን ሌላ ። ሲሞትም እንደቆመባት ቦታ ሁሉ ሌላ ሸክም ሆኖ ምድርን አጣባቢ ይሆናል በመቃብሩ ማለት ነው።

ወጣቱ ትውልድ ዛሬ የማካፍልህ እራስህ አንብበህ ሃቁን ልትረዳው ከምትችለው የሃቅ የታሪክ ማሕደር ተቀንጭቦ ከተሰጠኝ ሲሆን ይሄውም ለአንተም ላንቺም ፡ ለእኔም ነጻነትን ስላጎናጸፉን ጀግኖቻችን ከብዙዎቹ በታሪካቸው በጀግንነታቸው የመጀመርያ የጦሩ መእራፍ እና የጦሩ ገበሬ ከነበሩት የመቶ አለቃ ሃይለማሪያም ማሞን እና የደጃዝማች ፍቅረማርያም አባተጫንን ጀግንነት እና ውለታ ነው። አስታውስ በብሄር፡ በትውልድ ሃረግ፡ በክልል ሳይሆን የተዋደቁት በአንድ አገር ፡ በአንድ ሕዝብ እና በአንድ ሰንደቅ አላማ ስም ለማሉላት እናት አገራቸው እና ወገናቸው፡ ስንደቅ አላማችን ለእኔ ላንተ ላንቺ ነጻነት እንደነበር።

ወያኔ በመእራባውያን እና አረቦች እየተረዳ ወደ ቤተመንግስት ከመግባቱ አንድ አመት በፊት የአርበኞች ማሕበር በጊዜው በሕይወት ተርፈው ሳይደላቸው ባጎንጸፈኡት ነጻነት ደልቶት ተርፎት ጭምር የሚኖር ተመልካች ሆነው እየተራቡ ሲኖሩ የነበሩት እና የረባ እንክዋን እንቅል ሳይተኙ እንደው በሃሳብ ነገ ምን እበላ ይሆን እያሉ አንዳንዱም ማደሪያ እንክዋን አጥቶ በዚህ መልክ የሚኖሩት ለአርበኞች ማሕበር ጽሕፈት ቤት ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ማሕበሩን እነዚህ ጀግኖች እያስጎበኙኝ እያስረዱኝ ፡ እያስተማሩኝ ጉብኝቴን እጨረሳለሁ በቀኑ። ከዛም ከመሰናበቴ በፊት በእጄ ጀግኖቹ እራሳቸው ፡ ሽልማት የጀግኖች ታሪክ ከዚህ በታች ጥቂቱን ከመሃሉ የማቀርበውን ሁለት ቲኒንሽ እንደ ደብተር የተጠረዘ የእያንዳንዱን ጀግና ታሪክ ያሰፈረውን የታሪክ ክብር ያወርሱኛል ይሄውም በጊዜው ሱማሊ እናም የወጽት ጠላት ሕዝቡን እና ሰራዊቱን በአራቱም ማእዘን ጦርነት ገጥመውት ስላደረኩት አገሬ ገብቼ ከሰራዊቱ ጎን በመሰለፍ ካስፈለገም ለጦርነቱም ሰልጥኝ የዜግነት ግዴታዬን ለመወጣት ዝግጁ ስለነበርኩኝ ወደ አሜሪካን ለመመለስም ምንም ፍላጎትም አልነበረኝም። ያም ነበር ጀግኖቹን ከእኔ ጋር ያገናኛቸው። ሌላው የአጼ ቴዎድሮስ ፡ የንግስት ጣይቱ እና የጀግኖች ታሪክ በሃውልት የማሰራቱ ሕልሜ ትልቅ ስለነበረ ማለትም ቲኒሽ ሆኜ የሰማእታት መቃብር እየተባለ በሳጥን ተከምሮ ስላሴ በአብድ ክፍት መቃብር ውስጥ ካየሁት ጀምሮ በ13 አመት እድሜዬ ሁሌም ምኞት ነበረኝ እና ይሄንንም ለፕሬስ በሰጠሁት መግለጫ ሲሰሙ አስታዋሽ አገኝን በሚል ከሌላ ሳይሆን ከራሳቸው ከጀግኖቹ በመጣ ደግነት ተመርቄ በጊዜው ከነበሩት የጀግኖች ማሕበር ሊቀመንበር ቀኛዝማች ኢብሳ የመሃበሩ መተዳደሪያ ደንብ ተፈርሞ ተሰጥቶኝ በሽልማት መልክ ተሰነባብቼ ከጽህፈት ቤቱ ሕንጻ እወጣለሁ። የማይረሳኝ ጀግኖቹ እውጪ ድረስ ወጥተው የልባቸውን ችግር ካካፈሉኝ በሁዋላ ስላላቸው ችግር ከሁሉም የጀግናውን ታሪክ ሃውልቱን ማሰራቱን በቶሎ እንዳደርገው አሳስበውኝ እንለያያለን።

ከሶስት ቀን በሁዋላ ስልክ ይደውልልኝ እና ወደ ጀግኖች ማሕበር ጽህፈት ቤት ተመልሼ እንደሄድ ይነገረኛል ። ጥሪያቸውን አክብሬ በቦታው እገኛለሁ። ጀግኖች "የኢትዮጵያወርቅ ጋሻው "የጥናታዊ ኢትዮጵያ የጀግኖች ማህበር አለም አቀፍ እንደራሴ" መደረጌን እና የዜግነት ግዴታየም በአደራ መልክ ጭምር ሁለት ተግባሮችን በስራ እንዳውል ይነገረኛል። እኔም በደስታ ከዛ ሁሉ የፋሽስት ጦርነት አገሬን ሕዝቡን ነጻ አውጥተው እኔም ያለእናት ያለአባት በነጻነቴ አገሬ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደልቤ ያለመንም ክልል መወሰን እንዳደግ ነጻነቴን ባጎናጸፉኝ ጀግኖች የተሰጠኝ ሃላፊነት በደስታ ተቀበልኩት። በተግባር ለመተርጎምም ቅድሚያዬ አድርጌው ነበር። ይሄም ጥንታዊ ኢትዮጵያ የጀግኖች አርበኞች ማሕበር እንደራሴ ብሎ ግለሰብ አገር ወዳድ ሲሰይም በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ በመሆኑ ትልቅ ሽግር ሳይፈጠረብኝ ያለፈ እንዳይመስላችሁ። ሆኖም አስብበት እና ጉዳይ አስፈላጊ ከመሰለኝ አካፍላችሁዋለሁ። ይቀጥላል።