Friday, August 19, 2011

የቀድሞ ስራዊት አባሎች የሰራዊቱ እፍረቶች፡ ተፈራ ወርቅ አሰፋና ዮናስ ሊበን የተባሉት ለአመታት ሲክዱትና "ሃስት ነው የኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበሩን በዳላስ አላፈረስንም" እያሉ አሁን እውነት ነው ብለው በራሳቸው ላይ ሃሰተኞችን በቤተክርስቲያኑ እያመጣ በማናዘዝ በታወቀው በተአምረኛው የቅዱስ ሚካኤል ደብር ውስጥ መሰክረዋል።

እግዚአብሄርን የሚከተል በሱ የሚመራ የእውነት ተራራ ላይ ቆሞ ሃስተኞች በውሸት እስሳተጎሞራ ባህር ውስጥ ሲቀቀሉ ያያል!


ክርስቶስ፡ በሃሰት ወገን ላይ ለግል ጥቅም በኮሚቴ ተቀናጆ ከመፍረድና ከመመስከር ይሰውረን። ለተቸገረው ወገናችን ችግር ደራሽ እንጂ ከአፉ ነጥቀን ከመጉረስም ለልጆቻችንም ከማጉረስም ይጠብቀን። ለዘላለሙ አሜን!

 በቅዱስ ሚካኤል ደብር ጁላይ ሰላሳ አንድ አምላክ የሰራውን አንባቢያን ልብ በሉ። በተለይም የዳላስ ፎርት ውርዝ ንዋሪው ኢትዮጵያውያን ውነቱን ውሸት ነው ተብሎ ሲታለል የቆየው። በግላችሁ ለመፍረድ አትቸኩሉ የአምላክ ፍርድ የማይነቃነቅ የማይሞት ፍርድ ስለሆነ በውሸት የፈረዱባችሁና የመሰከሩባችሁ፡ አድማም የመቱባችሁና ለሃሰተኞችም ሻማ ያበሩ ሁሉ በአምላክ ፍርድ ቤት እነሱው በራሳቸው ላይ ፈርደው መስክርው ሲቀጣቸው ያሳያችሁዋልና። በቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በጋርልላድ/ዳላስ ጁላይ ሰላሳ አንድ የተሰማው ድምጽ የዮናስና የተፈራ ወርቅ ሲክዱት የኖሩት መረዳጃ ማሕበሩ ፈርሶ አልነበረም በሚል፡ አዎን የመረዳጃ ማሕበሩ ከሁለትሺ ሰባት ኦገስት ሃያ ዘጠኝ እስከ መስከረም ሁለትሺ ስምንት ድረስ ፈርሶ  ነበር ብለው በራሳቸው ላይ በሊቁ የዱስ ሚካኤል ደብር እንዲመስከሩ ክርስቶስ የወሰነው ፍርድ ነው። የአምላክን ስራ እዩት በእውነት ተፈራ ውርቅና ግብረአብሮቹ ኮንፍልሊክት ኦፍ ኢንትረስት ከቤተክርስቲያናችን ሰዎች ይውጡልን ብለው የቅዱስ ሚካኤልን ደብር ልክ እንደመረዳጃ ማህበራችን ሙርከኛ ለማድረግ ያላደረጉት ጥረት የለም። ከናካቴው ሚካኤልን ለማፈራረስ ምእመናኑንም ለመከፋፈል ምን ያላደረገው ነገር አለ ተፈራ ወርቅ? የአምላክን ደግነትና ፍርድ በብሎግ ትንተና ገለጻ ተወስቶ የሚታይ ሳይሆን፡  መጸሃፍ ቅዱስ አቅፎ ተንበርክኮ በመጸለይ የሚታይ ስለሆነ እግዚአብሄር እነዚህን ሕዝቡን ሲዋሹት የኖሩትን አጭበርባሪዎች በስሙ ነጋዴዎችን ደጋፊዎቻቸውን ምስክር አድርጎ በራሳቸው ላይ በሁለት ምላስ እንዲመሰክሩ ያደረጋቸው ሚስጢር አለው። ስለሆነም የጋራ መረዳጃ ማሕበሩን ለሁለት የድብቅ አላማ ሆነ ብለው ካፈረሱት በሁዋላ አምስት ጊዜ ደብዳቤ ሕብረተሰቡ ሳያውቅባቸው በትህትና ተጽፎ መረዳጃ ማሕበርንና የሬዲዮን ስርጭቱን ወይም ፕሮግርም እንዲሁም ዝግጅቱን እናድን ሲባሉ በስልክ እንክዋን መልስ ሳይሰጡ በማን አለብኝነት ልባቸው አብጦ በሃሰት "መረዳጃ ማሕበሩ አልፈረሰም ስማችንን በሃሰት ለማጥፋት ነው። የሪድዮን ፕሮግራሙን አዘጋችብን፡ የጋራ መረዳጃ ማሕበሩን ልታፈርስ ነው፡ የጋራ መርድጃውንና እኛን ቴረሪስቶች ናቸው ብላ ፍርድ ቤት ከሰሰችን አድኑን አውግዝዋት፡ ወደ መረዳጃ ማሕበሩ ወደፊት መጥታ ለሕብረተሰቡ አገልግሎት እንዳትሰጥ ወስነናል በሃሰት ስማችንን የሐረርወርቅ ስላጠፋች፡ አግልለናታል ከመረዳጃው ሕዝቡም ያግልላት ብለን ፈርደናል ፍርዱም በምረዳጃው አስቀምጠናል" በሚል አርባ ሁለት ሰዎች ያሉበት የውሸት ምስክሮች ኮሚቴ በማቁዋቁውም በእኔ ላይ ኮሚቴ አቁዋቁመው ጠቅላላ ጉባኤ በሚል ያንን ሁሉ "ወይዘሮ የሐረርወርቅ በተገኙብት!!!!!!!" በሚል የፈረዱትን በሬዲዮ በመፈራረቅ ከማንበብና ከመፈረጅ በሃሰት ቅንብርብር፡ ለምን ልክ አሁን እንዳመኑት የመረዳጃው ማሕበር መፍረሱን መረጃውን ጭምር እንዳስረከብክውቸው ጥፋታችንን እናርማለን መረዳጃው መልሶ ያጣውን ሕጋዊነቱን በእስቴት ኦፍ ቴክሳስ መልሶ እንዲያገኝ እናደርጋለን ቢሉ ኖሮ? መልስ ለእኔ እንደመስጠት ለጻፍኩዋቸው ደብዳቤዎ ለምንስ በሬዲዮ ወጥተው ኮሚቲ ፈጥረው ኮሚኒቲውን ልታፈርስ ነው አሉ? ምናለበት ሕዝቡን ቢያከብሩት  ለጥቅሙ ለሰላሙ ለአንድንቱ ቢወዱት?