Wednesday, September 7, 2011

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የስዴት መንግስት በግፍ አደጋ የደረሰባትን ኢትዮጵያዊት ሕክምና በአሜሪክን አገር እንድታገኝ ጠየቀ።

መልካም ኢድ ለእስልምና ተከታዩ ውገናችን ሁሉ።


አጭር ዜና።

በሊቢያ በፈላ ውሃ የተቃጠለችውን ኢትዮጵያዊት አስመልክቶ የሕክምና እርዳታ ከተለያየ አቅጣጫ እንዲደረግላትና ከተቻለም ወደ አሜሪካን ዳላስ ቴክሳስ መጥታ ሕክምና የምታገኝበትን መንገድ ጭምር እርዳታ አድራጊ ሆስፒታሎችን የኢትዮጵያ ብሄራዊ የስዴት መንግስት እያነጋገረና እያስተባበረ ስንብትዋል።  ከአዲሱም የሊቢያ ጊዜአዊ መንግስትና ከሃኪሙዋም  ጋር ግንኙነት ፈጥሮአል። የአሜሪካን መንግስት ቪዛ እንዲሰጣትም ሃሳብ የስዲቱ መንግስት አቅርብዋል፡ እያመቻቸላትም ይገኛል።

በዚህ አጋጣሚ መግለጽ የምንወደው ማሳሰቢያ በስማዋ ለሕክምናም ይሁን ለሌላ ወጭ ብለው ገንዘብ ለሚጠይቁ: ሕክምና እንጂ ገንዘብ አሁን አያስፈልጋትም።

አየለ ጉተማ
ከኢትዮጵያ የስዴት መንግስት ሕዝብ ግንኙነት
አትላንታ ጆርጂያ።