Sunday, July 31, 2011

ትናንት እድሩ እንዳይቁዋቁዋም ወረቀት ሲበትኑ የነበሩት የመረዳጃና የሬዲዮን አዘጋጆች ከጥቅም ተካፋዮቻቸው ጋር፡ ዛሬ ደግሞ ከመረዳጃ ማሕበሩ ስለተመነጠሩ፡ የእድር ተቆርቁዋሪ በመምስለ እድሩን እነሱ በሚፈልጉት ካልሆነ ለማፍረስ እየተርዋርዋጡ ነው። እድሩን አድኑት! እድሩ መፈጠሩ ጥሩ ነው እንደውም ሃሳቡን ያመጡት ቀደም ብለው ቢጀምሩት ጥሩ ነበር ዘግይትዋል ።



አምላክ የአለም ፈጣሪ ለእንዚህ ጥለውት ለሚሄዱት ከንቱ አለም በውጪና በአገር ቤት የሚኖረውን ሕዝብ እየጠቆሙና መረጃውን በመሰብሰብ ደሞዝ የሚከፈላቸውን የሴጣን ቁራጮች ያንተን ስም በሃቅ እንዲጠሩ አድርጋቸው አሜን!
እድሩን በቁጥጥራቸው ስር እንዳለ ለመኖር ትናናት ወረቀት እየበተኑ አይቁዋቁዋም ያሉት እነተፈራ ወርቅ፡ በትሩ ግርማ ንጉሴን ዘውግ፡ ዛሬ ደግሞ ሊፈርስ ነው በሚል አዲስ የተቁዋቁዋመው ቦርድ እድርተኞች ጨምሮ አስፋፍቶ ሊሰራ ባለበት ወቅት እድርተኛውን ሊያፈርሱልህ ነው በሚል እያወናበዱት ይገኛሉ።
እድርተኞች እድሩን ከመፍረስ አድኑት። እናንተን እንደ መያዣ ይዘው እነበትሩና ተፈራወርቅ ዘውገ ወደ መረዳጃ ማሕበሩ ለመመለስና የለመዱትን ፍሮድ ለመቀጠል ነው ይሄ ሁሉ መርዋርዋጥ። ፍሮዱ ተሰርትዋል ያግልጽ ነው እነዚህ ሰዎች ሊያጠፉ እንጂ ሊያለሙ የመጡ ሆነው አያውቁም። ለምሳሌ ከጥቂቱ ሃምሳ አራት ሺ ዶላር የመረዳጃው፡ እድር ሳይቁዋቁውም የነበርው በሁልትሺ ሰባትና ስምንት ከእድሩ መቶሺ፡ ዌል ፋርጎስ በየጊዜው አስራ አምስትሺ፡ ከሴፍኮ አስራአምስትሺ በድጋሚ ከካትቶክ ቻሪቲ ወዘተ ፍሮድ አዎን ፍሮድ ተሰርተዋል ከእድሩም ከመረዳጃ ማሕበሩም በማጭበርብር። ከግማሽ ሚሊዮን ያላነሰ የበሉ፡ ገንዘቡን ለዲኤፍ ደብልዩ ጠረቤዛ የከፈሉት ሳይቅር መመለስ አለባቸው የህዝብ ገንዘብ። እስቲ የትኛው ሰው ነው ፍሮድ አልሰሩም ብሎ የትኛው እድርተኛ ነው ፍሮድ አልስሩም ብሎ ሊያስረዳኝ የሚችል መቼ እሱስ አውቆት ሁላችንም ተጭበርብረናል ሕብረተሰቡ በሙሉ። 
ፍሮዱ እድርተኛው የፈጸመው ሳይሆን በመረዳጃ ማሕበሩ ስም የተፈጸመ ስለሆነ ያለፈውን ያሁኖቹ ለማረም እየሞከሩ ይመስለኛል። እነዚህን አሁን ቦርዱን የተረከቡትን ሕብረተሰቡ ወዶዋቸዋል አምኖባቸዋል ይተማመንባቸዋልም ነገር ግን እድርተኞችን ማስፈራሪያ አድርገው እነተፈራወርቅና በትሩ ከተቀመጠበት ድምጹን አጥፍቶ በእጁ ቀጥል አቁም አይነት ምልክት እየሰጠ በቦርዱ መሃል ሳይታወቅ በስህተት የገባውን ግለሰብ በመምራት የተለመደውን የሽሽግ የቦርዱ ሊቀመንበርነቱን ስራ ላይ ለማዋል ብዙ ሞክርዋል።
ዛሬ እሁድ ነው የእረፍት ቀኔ ነው ሆኖም የሕዝብ ጉዳይ ከራሴ የበለጠ አስቀድሜ የማየው በመሆኑ እንደተለመደው፡ ለጠየቃችሁኝ ጥያቄ እድሩ ፍሮድ ሰርትዋል ወይ ? እድሩስ በመረዳጃ ማሕበሩ ስር አብሮ ተጣምሮ ያለ አይደለም የሚል ባለፈው እሁድ በተደረገው ስብሰባ ላይ ገልጠሻል ወይ?
እንዴት ነው እድሩና መረዳጃው አብሮ አይደለም አልሽስ የተባለው? የሚል ጥያቅን የጨመሩ ጥያቂዎችና ሌሎቹም እንዳብራራላችሁ ጠይቃችሁኛል። አመሰግናለሁ ይሄ ትክክለኛ አቀራረብ ሲሆን ለአጭበርባሪዎች ፍሮድ ለሚሰሩትም ግለሰቦች እንዳይስፋፉና እንዳይንሰራሩ ሕዝብ እንዳይከፋፍሉ ስለሚያደረግ ይሄን አይነት ግልጽ ጥያቄ መለመድ ይኖርበታል በጣም አመሰግናለሁኝ ስለጠየቃችሁኝ ውነቱን ለመረዳት ከእኔ። ሁሉም ጠይቆ ቢረዳ ስለህብረተስቡ ጉዳይ ንቃት ይኖረን ንበር እንጂ መሳሪያ ተጎታች መጠቀሚያ አንሆንም ነበር።
ለዛሬ ልላችሁ የምችለው ተመሳሳይ ነገር ተፈረወርቅ፡ በትሩና ዘውገ ግብረአበሮቻቸው ግርማ ንጉሴ ለእናንተ እንዳሉት ሁሉ ላልደወሉልኝም ማለታቸው አይቀሬ ስለሆነ ሕዝቡን በማክበር ከዚህ በታች ያለውን መግለጫ ባጭሩ አቀርባለሁ ሰፋ አድረጌ ግን ሃቁን ከነማስረጃው አቀርባለሁኝ እንዳስፈላጊነቱ በቅርብ።
እነዚህ ግለሰቦች እንደሩ እንዲኖር በትክክሉ የማይፈልጉ ናቸው። ከአዲስ አበባም በሃምሳ ሁለት ገጽ የቀረበላቸው መመሪያ በዚህ መልክ በእየ ድርጅቱና ሕዝቡ በሚሰባሰብበት እየገቡ ሕዝብን መበታተን ስለሆነ እነ ዚህ ግለሰቦች ደሞዝ ከኤንባሲው የሚያገኙበትን ስራቸውን እየሰሩ ነው ያሉት ቁዋሚ ስራቸው ሕዝቡን በውጪ ያለውን የትግሬ ነጻ አውጪ የኢትዮጵያን ሕዝብ በክልል ከፋፋዩን አላማ ማስፈጸም ስለሆነ ይሄንንም ወደ ፊት በዚሁ ብሎግ በከፊል እየተደረገ ይወጣል ታዩታላችሁ ለማታውቁት ማለት ነው እንጂ ብዙ ወገን ያነበበው ነው። ጥሩ ምሳሌ በትሩ የመለስ መልክተኞች በመጡ ጊዜ ሆነ ብሎ እስሙም እንደሱው በስውር በድርጅት ስም የሚንቀሳቀሱት ጭምር የተጫወቱትን ቲያትር አንዱ የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው። ግንቦት ሰባት በትሩ የገባውም ግንቦት ሰባት የሚለውን የማፈራረሻ ዘዴ ለማጥናት ነው ያለውን ክፍተት።
እድሩን እነዚህ  ግለሰቦች እንዳይቁዋቁዋም በድብቅ ስብሰባ እያደረጉ ስማቸውን ሳያስቀመጡ ወረቀት ሲበትኑና በየዋህ ሰዎች ነገሩ ባልገባቸው በጊዜው በእውነት የጋራ ማረዳጃ ማሕበሩን ለማዳንና በእድር እንዳይተካ ታሰቦ መስልዋቸውና ቀባሪ ለሌለው መረዳጃ ማሕበሩ መቅበሪያ እንዲሆን በማሰብ በግርማ ንጉሴ አማካኝነት ይሰራጭ የነበረውን አንዴ ኮሚኒቲ ፎር ሴል በሌላ ጊዜ ማር የተለወሰ መርዝ ወዘተ በሚል በኤርፓርት ሳይቀር በስብሰባ እያሳተፋቸው አሳምኖ በሰጣቸው መሰረት አምነው ተቀብለው በግልጽ ቤተክርስቲያንና ታክሲ ወይም ኤርፓርት ጭምር ሲበትኑ ነበር። እንደውም አቶ ንጉሴን እድሩ እንዲቁዋቁዋም በጣም ይጥሩ ከነበሩ ታክሲ ነጂዎች ጋር መጣላታቸው ግልጽ ነው። ይሄ  ሁሉም ያየው ሲሆን ለዚህም መሳሪያ ካደረግዋቸው መሃል በጣም ሰው ሲቸገር እሮጦ የሚደርሰውን አቶ ንጉሴ ጋረድንና ወይዘሮ ቲና ካሳይን መጥቀስ ይቻላል ለማለት ነው።
ሆኖም የሚበተነው ወረቀት ላይ ለሕብረተሰቡ ተቆርቁዋሪዎች በሚል ብቻ በማስቀመጣቸው ወይዘሮ ቲናም ሰዎችን ስለምትረዳን አቶ ንጉሴም በቤተክርስቲያኑም ቢሆን አገልጋይ በመሆኑ ም እመናኑ የግራማ ንጉሴና የዘውገ ፡ የአመሃ መልክት በሚገባ ሲተላለፍ እነሱ ቆመው ያዩ ነበር ለሕዝቡ ለመሰራጨቱ ግባቸው። ከናካቴው እነሱ እራሳቸው ጉዳዩን እንደማያውቁ ሲቀበሉም ነበር።
በሚስጥር በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ ሴንትራል ኤክስፕሬስና ሮያል ቲንሺ ጽህፈት ቤት ውስጥ  እኔም በስብሰባቸው ላይ ተገኝቼ ተንኮላቸውን አየሁት።
 አመሃ የተባለው የቦረድ አባል ማለትም እራሱን ዶክተር አመሃ ነኝ በሚል ዶክተር ሆኖ የማይስራ  አንዱ እድሩ እንዳይቁዋቁዋም አድፋጭ ህዝቡን ለመከፋፍል የመከፋፈያ የነገር ደማሚት ቀባሪዎች መሃል ሲሆን አገሬ ኢትዮጵያም ይሄንን ስለሚያውቅ ከዛም መረዳት ይቻላል። ሆኖም እድሩን ለእድሩ የተነሱት ሲያድኑት፡እኔ ደግሞ የመረዳጃ ማሕበሩንና የሬዲዮን ስርጭቱን ከመነጠቅና ወደ ግል ጥቅም ለአዲስ አበባው መንግስት መሳሪያ እንዳይሆን አድኛለሁ በጊዜው።  የእነሱ እኔን ሬዲዮን አዘጋጅ፡ ቴረሪስት ብላ የመረዳጃ ማሕበሩና እኛን ከሰሰችን የክስ ወረቀት ደርሶናል ድረሱልን ብሎ በውሸት መብረቅ መተርከክና የጋራ መረዳጃ ማህበሩን በእነሱ አነጋገር ኮሚኒቲውን ልታፈርስ ነው ብለው በቡዋረቁት ጉዳዩ የሞተ ወይም ለፍርድ ቤትም ጊዜው ያለፈበት ቢመስላቸውም፡ ሃቁ ሃቅ ስለሆነ በሆቴል ካንጋሩ ፍርድ ቤት ስብሰብ እኔን ለመጉዳት አርባ ሰዎች ኮሚቲ ብለው ፈጥረው ቢዋዥቁም ፍንክቺም አላልኩኝም። ለዚሁም ባለፈው እሁድ በጁላይ ሃያ አራት በመረዳጃ ማሕበሩ ጥሪ በተደረገው ሕዝባዊ ስብሰባ ተገኝቼ መረዳጃ ማሕበሩን ለሁለት የድብቅ አላማቸው አፍርሰውት እንደነበረና በሁለትሺ ሰባት እነዚህ በእኔ ላይ የትግሬ ነጻ አውጪ ተቀጣሪዎች ያወረዱት ውርጂብኝና ፍረጃ ፡  መረዳጃ ማህበሩንና ሬዲዮኑን ልታዘጋ ያሉት ውሸት መሆኑን ገልጬ ሰነዱን መረዳጃው በኦገስት ሃያዘጠኝ ሁለትሺ ሰባት ፈርሶ መስከረም አስራ አምስት ቀን ሁለትሺ ስምንት ማለትም እኔላይ ያንን ሁሉ ወርጅብኝ ባወረዱና ፈረድንባት በጠቅላላ ጉባኤ ባሉ በዘጠንኛው ወር ወደው ሳይሆን ያሰቡትን አላማ እነሱም ይሁኑ የትግሬ ነጻ አውጪ ተፈጻሚ እንዳያደርጉት በማድረጌ ሳይወዱ በግድ ሪንስቴት ወይም መልሶ መረዳጃ ማሕበሩ ሕጋዊነቱና እንዲያገኝ በስቴት ኦፍ ቴክሳስ ያደረኩበትን በስብሰባው አዳራሽ በተሰበሰበው ሕዝብ ፊት ለአዲሱ ቦርድ አባላት አስረክቤለሁ።
ፍሮድ ሰርቶ በመኖር የሚታወቁት ከእነ ደጋፊዎቻቸው ጭምር ባሉበት ሳስረክብ ጪጭ ከማለት ሌላ አንዲትም ቃል ያለመተንፈሳቸውን ከቦርዱና እራሳቸውን ሲክቡዋቸው ከነበሩት መስማት ይቻላል። የሬዲዮን ስርጭቱም እንዳላዘጋሁኝ ሽንጤን ገትሬ ተናግሬአለሁ። ተፍራወርቅንም የመረዳጃ ማሕብሩን ገንዘብ በፍሮድ እንደበላው ከእነ ግብረአበሮቹ ሕዝብ ፊት ለማንም አንገቴን ሳልደፋ ተናግሬአለሁ 
የታደረከው ገንዘቡን? ብዬም ጠይቄአለሁኝ።
በመጨረሻም ለዛሬ ለጥያቄያችሁ ይረዳ ዘንድ፡
እኔ ሳልሆን መረዳጃ ማሕበሩ ከእድሩ ጋር እንዳልሆነ መልስ የሰጠው
በስብሰባው ላይ በእድርተኛ ለቅረበልት ጥያቄ የእድሩ ሊቀመንበር ነው የተባለው ነው።  ስለ እድሩ ልጠየቅም ለመልስም አልችልም እድሩ ውስጥ የለሁበትም እስከዛሬ ስለ እድሩ ምንም አይነት ጥያቄ ኖሮኝም አላውቅም ስለመረዳጃ ማሕበሩ ብቻ እንጂ። እድሩ እንዲቁዋቁዋም ከመደገፍ ሌላ አይቁዋቁዋም ብዬም አላውቅም መክኒያቱም ማንም እድር ማቁዋቁዋም መብቱ ነው። እኔም እድር የማቋቁዋም መብት እንዳለኝ ሁሉ።
ሲበተን ስለነበረው ወረቀትና ለምን እድሩ እንዳይቁዋቁዋም እንደጣሩ በጊዜው፡ ከዛም  እንዴት እድሩን ለይስሙላ ብቻ በመረዳጃ ማሕበሩ ስር ነው እያሉ ፍሮድ እየሰሩ እድርተኛውም ሕብረተሰቡም ሳያውቅ እስከወጡ ድረስ እንደኖሩ ማለትም አንድም ሰው ሳይረዱበት ገንዘቡ ሙልጭ ብሎ ሃምሳ አራት ሺው የራሱ የመርዳጃ ማሕበሩ እድሩ ሳጀመር በፊት ያለውን ጭምሮ ገንዘብ ከካቶሊክ ቻሪቲ ተሰጠን ያሉት ጭምር ያለወጪ እንደጠፋና ከትግሬ ነጻ አውጪ መግስት ሃምሳ ሁለት ገጽ መመሪያ ይዘው በመሃላችን ኢንፎርሜሽናችንን እያወጡ ከእድሩ የሚገኘውን ጭምር አደጋ ላይ ሕዝቡን እንዳጋለጡት ሰፋ አድርጌ ስለምጽፍ ለዛሬ ግን እድርተኛው መሳሪያቸውና ማስፈራሪያቸው አድርገውት ሕዝቡን ሰላም እንዳያገኝ እየተጠቀሙበት ስለሆነ
እድርተኛው እንዲጠነቀቅ አሳስብለሁ። እድርተኛውም ለእድሩ ችግር ፈጣሪዎች ናቸው በሚል ስለሚነጋራቸው ሰዎች እየደወሉ ችግራችሁ ምንድነው? ብለው ቢጠይቁ አንድም ሰው እድሩን እንደማይቃወምና የማንም ጉዳይ እንዳልሆነም ይረዱታል። በዚህ አይነት መንገድ ብቻ ነው ሰላማቸውን ሊያገኙና ሁላችንም የእድሩ አባላት ልንሆን የምንችለው።
እድርተኛውን በዛሬው ስብሰባ በሚካኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ለማበጣበጥና ሃሰትም ለማስተጋባት እንደተዘጋጁ ከላይ እንደገለጽኩት ጥያቄ የጠየቁኝ ወገኖቼ ባሰረዱኝ መሰረት ደርሼበታለሁ። እነዚህ ሰዎች አልቆላቸዋል መረዳጃ ማሕበሩን በሚመለከት ነገር ግን እድሩን ለመቆጣጣርና ግባቸውን ለመምታት የማይፈነቅሉት ድንጋይ ስለሌለ እድርተኞቹ እድር ውስጥ ካልገባው ወደ ሰላሳሺ ከሚሆነውም ወገን ጋር መጋጨት እንዳይሆንባቸው እላለሁ።
 እኔን በሚመለከት እድርተኛው በማንኛውም ጊዜና ሰአት ቀደም ብሎ ነግሮኝ ስብሰባ ቢጠራኝ እራሳቸው ሌቦቹ ባሉበት ለማስረዳት ዝግጁ ስለሆንኩኝ ችግር የለውም። እድሩን የምደግፍ መሆኔን ደጋግሜ እንደገልጽኩት አሁንም በድጋሚ እደገና ማረጋገጥ እወዳለሁ። በጁን አምስት በዴኒስ ሬስቶራንት ለኢትዮጵያ ቀን ዝግጅትን አስመልክቶ በተጠራው ስብሰባ በተገኘሁበት የእድሩ ጸሃፊ እየሰማ እድሩን እስከ ሶስትሺ ብሎም አምስትሺ ድረስ ባጭር ጊዜ እንዴት ልናደርሰው እንደምንችልና ሕግን በማይንጻረር መንገድ ሕብረተሰቡንም አደጋ ላይ በማይጥል እድርተኛውንም መረዳጃ ማሕበሩንም በሚረዳ መልኩ ሊሰራ እንደሚቻል  በስብሰባ አነጋግሩኝ ማለቴም እድሩን ስለምደግፍ ነው። እድሩን የምቃወም ቢሆን እቃወማለሁ እላለሁ ስለማልቃወም ግን ትቃውማለች እያሉ አጀንዳ በእድር ለማስያዝ መርዋርዋጥ ግን የእኔን ስም እየተጠቀሙ እድሩን ልክ ባልፈው እሁድ መረዳጃ ማሕበሩን አዲስ ቦርድ በእድርተኞቹ በመጠቀም አውርዶ በቁጥጥራቸው ስር ለማድረግ እንደጣሩትና እንደከሸፈባቸው እድሩን በቁጥጥራቸው ስር ለመመለስ የሚያደርጊት ጥረት ነው። እኔ ሳልጠየቅ መልስ ሳልሰጥ አንድ ቃል ይዞ መሳሪያ የሚሆኑ ሰዎች የሐረርወርቅ ይሄን አለች ያን አለች ፡
ወሬ አናፋሽነታቸውን እንጂ ወንድነታቸውን አይደለም የሚገልጹት እድሩን በሚገባ የምደግፍ መሆኔን በድጋሚ በተደጋጋሚ እገልጻለሁ። ጊዜ ወስዳችሁ መወናበድ ስልችቶዋቸው ለደወላችሁልኝ ትልቅ ምስጋና አቅርባለሁ። ወሬ አናፋሹም እንደእናንተ ልብ ኖሮት ጠይቆ መረዳትን እንዲማር እጸልይለታለሁ።

 ላንባቢያንም ከምስጋና ጋር ፡
የኢትዮጵያወርቅ (የሐረርወርቅ) ጋሻው።
 ዘብሄረ አንድ ኢትዮጵያ አንድ ሰንደቅ አላማ አንድ ሕዝብ።