Tuesday, July 26, 2011

"የኢትዮጵያ ቀን 2011 በዳላስቴክሳስ አዘጋጅ ኮሚቲ"

"Ethiopian Day 2011 Organizing Committee"
     Yeharerwerk Gashaw
         Chairperson
  


        ይችን ጥሩ ቀን ለፈቀደልን ምስጋና ለሁሉም ስልጣንና ወሳኝነት ላለው ለልኡል እግዚአብሄር ይሁን። አሜን። 
 
ዛሬ የቅዱስ ገብረኤል ቀን ነው። መልካም የገብረኤልቀን ያድርግልን።

አንባቢያንና ለኢትዮጵያ ቀን እንድናገለግል የመረጣችሁን በጠየቃችሁን መሰረት ባጭር ጊዜ ውስጥ ያከናወንናቸውን እነሆ።
በጁን አምስት ማለትም አንድ ወር ሃያአንድ ቀን ሆነው ማለት ነው የኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበር ቦርድ በይፋ ለዚህ አመት የኢትዮጵያ ቀን በአል አዘጋጅ ኮሚቲ  ለማስመረጥ በጠራው ስብሰባ ላይ ጥሪ አክብረን በቦታው ተገኝተን በመጨረሻም ሰባት ሰዎች ተመርጠን ሁለቱ ወንድሞች በስብሰባ ባይሳተፉም አምስት የቀረንው የሰራንውን ኢሜል እያደረግንላቸው ካስታወቅን በሁዋላ አንዱ የስብሰባው ቀን ይቀየርልኝ ባሉት መሰረት ብንቀይርም ከተመረጥን በሁዋላ አንድም ስብሰባ ላይ ሳይገኙ ቀርተዋል። ሌላው ቀደም ሲል በደረሰባቸው አደጋ መክኒያት ከኮሚቲው ጋር ለመስራት በየጊዜው በስብሰባ ለመገኘት  እንደማይችሉ ገልጸዋል። ሁለቱም ከኮሚቲው ለቀናል የሚል ደብድቤ ግን አልጻፉልንም። ሆኖም አምስት የኮሚቲ አባል ስራውን ስራውን ባጭር ጊዜ ለቦርዱ አቅርበናል። ተጨማሪ አስራ አምስት ሰዎችና ሰላሳ ልጆችም መዝግበን ለመጨመርም እየስራን ነው።

-----Original Message-----
From: yehar9 <yehar9@aim.com>
To: sesaxy <sesaxy@gmail.com>
Sent: Mon, Jun 13, 2011 6:16 pm
Subject: Ethiopian Day 2011 Organizing Committee meeting out come report to MAAEC

የዚህ አመት የኢትዮጵያ ቀን "የኢትዮጵያ ወጣቶች በአል" ብለንዋል። ወጣቱ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን አዘጋጅ ኮሚቲውን በሙሉ የሚመራው አድርገን አዘጋጅተንዋል። ፊልም ፕሮዲስሮችና ዳሬክተሮች "ዳላስ" የሚለውን በአለም የታወቀውን የቴሌቪዢን ሾው የሰሩ ሳይቀሩ ልጆቹን እድል ይሰጣሉ ለሁለት ሳምንት ኦገስት ውስጥ። ልጆቻችን ከእኛ ሕብረተሰብ ወጣ ብለው ብዙ ነገሮች ላይ ሊያሳትፍቸው የሚችል በር ልንከፍትላቸው ይገባል!
Ethiopian Day 2011 Organizing Committee
Dallas, Texas
በአቶ ስዩም የሕዝብ ግንኙነት አማካኝነት
ይድረስ ለኢትዮጵያ መረዳጃ ማሕበር በዳላስ ፎርት ወርዝ።

June13,2011

Subjec፡ meeting and out come report. ስብሰባችንና ውጤቱ ከአጭር ማሳሰቢያ ጋር በማጣመር.

በመጀመሪያ ትልቅ ሰላምታና ምስጋና ለኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበር አስተዳደር ስናቀርብ ከአክብሮት ጋር ነው። እኛንም አስመርጣችሁ ሃልፊነቱና ይሰራሉ ብላችሁ እምነቱንም ስለጣላችሁበን ስለ እምንታችሁ በጣም እናመሰግናለን። ስራውንም እራሳችን ሰርተን ማንም ከሁዋላ ልብሳችንን ይዞ በዚህ ሂዱ በዛ ስሩ ሳይለን ችሎታችንንና አስተዋጽዎቻችንንም ታማኝነትን ለሕዝቡ ጥቅም ብቻ የተራብን መሆናችንን ጭምር የምናሳይበት በነጻነት የምንሰራበት መድረክ ስለሰጣችሁን በዚህ በዳላስ ፎርት ወርዝ አንድነቱንና ሰላምን አጥቶ በየት የአንድነት ሜዳ እንደሚገናኝ ግራ የገባው ወገን ስምና በራሳችንም እያመሰገነን ይሂንን ቀጥተኛ አሰራራችሁን በማጠናከር ቀጥላችሁ ወደ ፊትም በከተማው ለሚኖረው ሕዝባችን ጥሩ አራአያ ሆናችሁ የአንድነትና የኢትዮጵያዊነት የጨዋ ጸባይን የጠፋውን በተለያየ መልኩ የክብር ችቦ አብርታችሁ በዳላስ ከተማ ላለው ወጣት እንደምታስረክቡ ተስፋ ጥለንባችሁዋል።
  የትናንትናው ጁን አስራ ሁለት ስብሰባና ውጤቱ ባጭሩ፡
ትናንትና ባደረግንው ስብሰባ በጣም ጥሩ ውጤት አምጥተናል። ተነድፈው በቀረቡት አሳራ ሃንድ የተግባር ኮሚቲ ላይ ስለ እያንዳንዱ የኮሚቲ ተግባርና ምን ያህል ሰው ለእያንዳንዱ ተግባር ማከናወኛ እንደሚያስፈልግ ጭምር ተነጋግረን ቀጥሎም በሻለቃ ሱራፌል የቀረበውን የሽልማት ኮሚቲ በአስራ ሁለተኛ ኮሚቲነት አስቀምጠንዋል። ለእያንዳንዱም የተግባር ስራ አምስት አምስት ሰው ልንመድብ ተስማምተናል። ለዚሁም እያንዳንዳችን አስር አስር ሰው መልምለን በሚቀጥለው ስብሰባ ካሳተፍን በሁዋላ እያንዳንዱ በበጎ ፍቃድ ተሳታፊ ምን ያህል ሰአት በቦታው ላይ እንደሚቆይ እና በእየ ሁለት ሰአቱ ወይም መቀያየር እንዳለበት ጭምር ወስነናል። አምስት ሰው ጠዋት አምስት ሰው ከሰአት አምስት ሰው ማታ እንደ ማለት ነው። ይሄውም ሁሉም የበአሉ ደስታ ተቁዋዳሽ እንዲሆን ሲሆን ከእነ ቤተሰቡ በአስተናጋጅነት ብቻ አይሰማውም በነገራችን ላይ ፡ የዚህ አይነት አስራር የተለምደ አልነበረም በመረዳጃ ማሕበሩ።የበአሉን ዝግጅት በተራ ተከተል ይሄውም ከመጀመሪያው ቀን መክፈቻ እስከ መዝጊያው ያለውን በዝርዝር በተራ ተከተል ለማቅረብ የእናነተ ሃሳብ መጨመር ስላለበት ከዚህ በታች ባስቀመጥነው ኮሚቶዎች ላይ የሚጨመር ኮሚቲ ካለ ጨምራችሁ እንድትልኩልን በኢሜል ወይም፡ ባለው እኛ የዝግጅቱ ኮሚ የተስማማንበትን ኮሚቲ ተስማምተናል ካልችሁም መልሳችሁን በዚህ ሳምንት መጨረሻ ድረስ ማለትም በጁን አስራ ስምንትና አስራ ዘጠኝ ድረስ ካስታወቃችሁን በኛ በኩል የኢትዮጵያን ቀን አስረኛ አመት ዝግጅት አጠናቀን ስራውን ለመጀመር በተግባር ይረዳ ዘንድ ልናቀርብላችሁ ዝግጁነን። ይሄንን ስንል የበአሉ አዘጋጅ ኮሚቲ እንደሚያስበውና እንደተዘጋጀ ከሆነ በጁን መጨረሻ ለእስፓንሰር ደብዳቤ መላክና በነብስም በቦታው በመገኘት እርዳታ የሚያበረክቱ ድርጅቶችን ጭምር ማነጋገር የምንጀምርበት ይሆናል። ማለትም ጁላይ ገንዘብና እርዳታ የምናገኝበት መጀመሪያው ሲሆን ከዛም ጎን በአሉንና ተሳታፊዎችንም ሕዝቡንም የምናነጋግረበት ይሆናል።
ቦታ ቶሎ መያዙ እስፓንሰር ለማብዛት ስለሚያስችለን በተለይ ፌር ፓርክ ቢደረግ በአሉ ይሄ ለአስራ አምስት አመት ከአሜሪካን ሕብረተሰብና ከውጪው እንዳይገናኝ ተደርጎ የኖረው የኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበር ልቆ የሚታይበትና ለምሳሌ ታክሲ ነጂዎቹን ብንወስድ ሕብረተሰባችን በመረዳጃ ማሕበሩ ስም በብዙ መልኩ በከተማው ከመንግስት መስሪያ ቤት እከ እያንዳንዱ የዳላስ ፎርት ወርዝ ህብረተሰብ እንዲሳተፍ በማድረግ ትልቅ ስም ይሰጠን የነበረውን አጥቶ ታክሲ ነጂው ሲቸገር አንድ የመረዳጃ ማሕበር የታወቀ ባለመኖሩ ነበር በአሜሪካን ጋዜጠኞችና በሕዝብ ተመርጠው ስልጣን በጨበጡት በኩል ድምጽ ልናሰማ ሃይል የምንሆን ኢትዮጵያውያን ተፈልገን የተጠራንውና ያስተጋባንው። ታዲያ አንድ ታዋቂ ኢትዮጵያዊት ይልቅ የኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበርና ታዋቂ ቢሆን በበለጠ ክብር የለውም? ይሄን ለማድረግ እጃችሁ ላይ ነው ውሳኔው ወገኖች። ስለዚህ በየስርቻው በቀን አምስት ሺ እየተከፈለ ምንም ለውጥ ለሕብረተሰቡ በማያመጣ ስርቻ ሲደረግ የነበርው የኢትዮጵያ ቀን መንግስት በሚያስተዳድረው ፌር ፓርክ ቢደረግ ብዙ ጥቅም አለው። ለምን ታንክስ ጊቪንግ ይደረጋል የሚሉት እራስ ወዳዶችንም ቢሆኑ ያልደፈሩት ለኢትዮጵያውያን አኩሪ ቦታና ባንዴ ስማችንን ክብራችንን የምናስመዘግብበት ቦታና በአል ነው ፌር ፓርክ ማድረጉ። ቶሎ ከወሰናችሁ በዛሪና በነገው ውስጥ እስፓንሰር ላይ ብቻ ነው ሁላችንም የምናቶክረው ፌር ፓርክ ከሆነ ማንም ኮርፓሬሽን እስፓንሰር ያደርጋል። የበአል ዝግጅት ቦታና የሕብረተሰቡን ብዛት ስለሆነ የምንሸጠው ለእስፓንሰሮች በድጋሚ በተደጋጋሚ ፊር ፓርክ የኢትዮጵያ ቀን የአስረኛው  በአል ቦታ ቢሆን ይመረጣል። ለምሳሌ የከተማውን ከንቲባና አማካሪ፡ የአሜሪካን ምክር ቤት አባላትንና ዳኞችን የኢሚግሬሽን ዳሬክተርንና ታዋቂ የሰው ልጅ መብት ተከራካሪዎችን ጭምር ብሎም እንደ ጄሪ ጆንስ የዳላስ ካው ቦይ ባለቤትን ብሎም ተጫዋቾቹን ለመጋበዝ ቦታው የመጀመሪያው ጥያቄ ይሆናል። አስቡበት በዚህ ዝግጅት ገንዘብ ከውጪው ድርጅቶች ለማግኘት መሆን ይኖርበታል አላማችን። መልሳችሁን የምንጠብቀው በቅርብ የኢትይጵያ ቀን አዘጋጅ ኮሚቴ።
ከአክብሮት ጋር በኮሚቲው ስም፣
የኢትዮጵያወርቅ (የሐረርወርቅ) ጋሻው።
ሊቀመንበር።
ከሕብረተሰቡ ገንቢ አስተያያት ከተሰጡት ሁለቱን ብቻ፡
ለብዙ አመት የኢትዮጵያ ቀን በአል ቀኑ ሲደርስ ኑና ስሩ በሚል ብቻ እየተጠሩ ሲያገለግሉና እንደ ቆሻሻ ወረቀት ሲጣሉ ተረስተው ነገር ግን አመቱ እንደገና ሲመጣ ብቻ የሚታወሱት ከዚህ በታች የሰጡትን አስተያየት እነሆ፡
በቀኑ ከእኛ ጋር ከተሰበሰቡት "አሁን በስብሰባው ተገኝቼ ካገኘሁት በተግባር መምጣቴን ተደሰትኩበት። መክኒያቱም ምንም እንክዋን ለብዙ አመት ለኢትዮጵያ ቀን በበጎ ፍቃድ ሳገለግል ብቆይም አንድም ቀን እንደዚህ እንደዛሬው ስብሰባ ተጠርቼ ገንቢ ሃሳብንና ለሕብረተሰቡ የሚጠቅመውንና የማያስፈልጉና የማያስፈልጉ ተግባሮች ላይ ህሳብ ስጥቼ የእኔም ሃሳብ በበአሉ ዝግጅት ውስጥ ገብቶ ስራ ላይ ውሎ ላይ ይቅርና ምን ታሰባለህ ብሎ እንክዋን አክብሮ ጠይቆኝ የሚያውቅ አንድም የመረዳጃ ማሕበሩ አባል አልነበረም። ዛሬ ግን በተሰጠኝ ያገባህልና ምከርበት በዝግጅቱ ተብዬ ሃሳቤን ለመስጠት በመቻሌ የኢትዮጵያ ቀን በአል አዘጋጅና የመረዳጃው ማሕበርም ባለቤትነት ስሜት እንዲኖረኝ አድርጋችሁኛል ስለሆነም ለመረጡዋችሁና ላስመረጣችሁ ለመረዳጃ ማሕበራችን አዲስ ተመራጮች ንገሩልኝ" ብለው ላለፈው ስድስት አመት ከተካፈሉት የኢትዮጵያ ቀን በመነሳት መታረም ስላለባቸውና ሌላው ቢቀር ቲኒሽ የምስጋና ደብዳቤ ወይም ሰርተፍኬት እንዲዘጋጅ ጭምር መደረግ ያለበትን በተግባር ኮሚቴ አሰራር ውስጥ እንዲገባ ባቀረቡት የነጻ ሃሳብ መግለጽ በደስታ ተቀብለን መዝግበንዋል።
ሁለት ወጣት ሴቶች ለብዙ አመት በኢትዮጵያ ቀን የተካፈሉት ለቦርዱ እንዲተላለፍ ከጠየቁን፡
እኛ በጣም የሚያሳዝነና በዚህ አመት መካፈል የማንፈልገው አንድ ነገር አለ ይሄውም፡ ልክ የኢትዮጵያ ቀን ሲዳረስ ሁለት ሳምንት ሲቀረው መጥታችሁ ደንሱ እንባላለን በቤተክርስቲያን በኩል። ነገር ግን ምን እኛን እና ጉዋደኞቻችንን እንደሚያስደስተንና ሊሰበስበን እንደሚችል የሚጠይቀን አንድም አላይየም ከእነ ቤተሰቦቻችን ጭምር ሄዱና ተካፈሉ የኢትዮጵያን ቀን በአል ዝግጅት ከመባል ሌላ።  ለምሳሌ ባለፈው አመት የተደረገበት ቦታ እንክዋን መንገድ በደንብ ለማያውቅ ኢትዮጵያዊ ይቅርና ለእኛ ለወጣቶቹ እንክዋን የነበረው ችግር በጣም አሳዝኖናል። እልም ያለ ይሄ ነው ሊባል የማይችል ቦታ አንዴ ስህተት ተደርጎ ከታለፈ ለመመለስ አስቸጋሪ የነበረበት ነው።
አንደኛ ቀረብ ያለና ወጣቱን ድግሞ የሚያሳትፍ ካልሆነ በዛ ላይ ልጆች ሁሉ በሃይማኖት ስም እንድንከፋፈል አድርገዋል ቤተሰቦቻችን ጭምር የመረዳጃውም ተጠሪዎች ፈጽሞ ከወጣቱ ጋር ግንኙነት የሌላቸውና እዛም ስንሄድ ክብር አይሰጡንም ፓሊስም ይጠርብናል አንዳንዲም። እንደዚያ ሳይሆን በደንብ የምታሰባስቡን ከሆነ እንሳተፋለን በተለይ ለሞደሊንግን ኮሜርሻል ፊልም ለመስራትም ስለምንፈልግ እድሉን የሐረርወርቅ እንደምትከፍትልን ካለፈው አፎሚያን ኒኮሎዲያን ላይ ስላየናት እየጉዋጉዋን ነው። እድሉን ያገኘችው በየሐረርውርቅ በተዘጋጀው ሾው መሆኑንና እስኮላርሺም እንዳገኘችው ሁሉ፡በሚል ደመደሙ ገንቢ ሃሳባቸውንና ምኞታቸውን ። 

Ethiopian Day 2011 Organizing Committee
Steering Committees

1.Sponsors/Support Committee
2.Venders/ID Committee

3.Silent Auction

4.Finance/Membership drive Committees

5.Entertainment Committees

6.Souvenir Booklet/Programs

7.Media/Public Relations/Community Relations

8.Children Village

9.Schedule & Super Vising Committee

10.Volunteer & Hospitality Committees Security

11.Guest Coordinating and Feed Back-Task as needed Committee

12. Honoring Committee