Sunday, July 31, 2011

ትናንት እድሩ እንዳይቁዋቁዋም ወረቀት ሲበትኑ የነበሩት የመረዳጃና የሬዲዮን አዘጋጆች ከጥቅም ተካፋዮቻቸው ጋር፡ ዛሬ ደግሞ ከመረዳጃ ማሕበሩ ስለተመነጠሩ፡ የእድር ተቆርቁዋሪ በመምስለ እድሩን እነሱ በሚፈልጉት ካልሆነ ለማፍረስ እየተርዋርዋጡ ነው። እድሩን አድኑት! እድሩ መፈጠሩ ጥሩ ነው እንደውም ሃሳቡን ያመጡት ቀደም ብለው ቢጀምሩት ጥሩ ነበር ዘግይትዋል ።



አምላክ የአለም ፈጣሪ ለእንዚህ ጥለውት ለሚሄዱት ከንቱ አለም በውጪና በአገር ቤት የሚኖረውን ሕዝብ እየጠቆሙና መረጃውን በመሰብሰብ ደሞዝ የሚከፈላቸውን የሴጣን ቁራጮች ያንተን ስም በሃቅ እንዲጠሩ አድርጋቸው አሜን!
እድሩን በቁጥጥራቸው ስር እንዳለ ለመኖር ትናናት ወረቀት እየበተኑ አይቁዋቁዋም ያሉት እነተፈራ ወርቅ፡ በትሩ ግርማ ንጉሴን ዘውግ፡ ዛሬ ደግሞ ሊፈርስ ነው በሚል አዲስ የተቁዋቁዋመው ቦርድ እድርተኞች ጨምሮ አስፋፍቶ ሊሰራ ባለበት ወቅት እድርተኛውን ሊያፈርሱልህ ነው በሚል እያወናበዱት ይገኛሉ።
እድርተኞች እድሩን ከመፍረስ አድኑት። እናንተን እንደ መያዣ ይዘው እነበትሩና ተፈራወርቅ ዘውገ ወደ መረዳጃ ማሕበሩ ለመመለስና የለመዱትን ፍሮድ ለመቀጠል ነው ይሄ ሁሉ መርዋርዋጥ። ፍሮዱ ተሰርትዋል ያግልጽ ነው እነዚህ ሰዎች ሊያጠፉ እንጂ ሊያለሙ የመጡ ሆነው አያውቁም። ለምሳሌ ከጥቂቱ ሃምሳ አራት ሺ ዶላር የመረዳጃው፡ እድር ሳይቁዋቁውም የነበርው በሁልትሺ ሰባትና ስምንት ከእድሩ መቶሺ፡ ዌል ፋርጎስ በየጊዜው አስራ አምስትሺ፡ ከሴፍኮ አስራአምስትሺ በድጋሚ ከካትቶክ ቻሪቲ ወዘተ ፍሮድ አዎን ፍሮድ ተሰርተዋል ከእድሩም ከመረዳጃ ማሕበሩም በማጭበርብር። ከግማሽ ሚሊዮን ያላነሰ የበሉ፡ ገንዘቡን ለዲኤፍ ደብልዩ ጠረቤዛ የከፈሉት ሳይቅር መመለስ አለባቸው የህዝብ ገንዘብ። እስቲ የትኛው ሰው ነው ፍሮድ አልሰሩም ብሎ የትኛው እድርተኛ ነው ፍሮድ አልስሩም ብሎ ሊያስረዳኝ የሚችል መቼ እሱስ አውቆት ሁላችንም ተጭበርብረናል ሕብረተሰቡ በሙሉ። 
ፍሮዱ እድርተኛው የፈጸመው ሳይሆን በመረዳጃ ማሕበሩ ስም የተፈጸመ ስለሆነ ያለፈውን ያሁኖቹ ለማረም እየሞከሩ ይመስለኛል። እነዚህን አሁን ቦርዱን የተረከቡትን ሕብረተሰቡ ወዶዋቸዋል አምኖባቸዋል ይተማመንባቸዋልም ነገር ግን እድርተኞችን ማስፈራሪያ አድርገው እነተፈራወርቅና በትሩ ከተቀመጠበት ድምጹን አጥፍቶ በእጁ ቀጥል አቁም አይነት ምልክት እየሰጠ በቦርዱ መሃል ሳይታወቅ በስህተት የገባውን ግለሰብ በመምራት የተለመደውን የሽሽግ የቦርዱ ሊቀመንበርነቱን ስራ ላይ ለማዋል ብዙ ሞክርዋል።
ዛሬ እሁድ ነው የእረፍት ቀኔ ነው ሆኖም የሕዝብ ጉዳይ ከራሴ የበለጠ አስቀድሜ የማየው በመሆኑ እንደተለመደው፡ ለጠየቃችሁኝ ጥያቄ እድሩ ፍሮድ ሰርትዋል ወይ ? እድሩስ በመረዳጃ ማሕበሩ ስር አብሮ ተጣምሮ ያለ አይደለም የሚል ባለፈው እሁድ በተደረገው ስብሰባ ላይ ገልጠሻል ወይ?
እንዴት ነው እድሩና መረዳጃው አብሮ አይደለም አልሽስ የተባለው? የሚል ጥያቅን የጨመሩ ጥያቂዎችና ሌሎቹም እንዳብራራላችሁ ጠይቃችሁኛል። አመሰግናለሁ ይሄ ትክክለኛ አቀራረብ ሲሆን ለአጭበርባሪዎች ፍሮድ ለሚሰሩትም ግለሰቦች እንዳይስፋፉና እንዳይንሰራሩ ሕዝብ እንዳይከፋፍሉ ስለሚያደረግ ይሄን አይነት ግልጽ ጥያቄ መለመድ ይኖርበታል በጣም አመሰግናለሁኝ ስለጠየቃችሁኝ ውነቱን ለመረዳት ከእኔ። ሁሉም ጠይቆ ቢረዳ ስለህብረተስቡ ጉዳይ ንቃት ይኖረን ንበር እንጂ መሳሪያ ተጎታች መጠቀሚያ አንሆንም ነበር።
ለዛሬ ልላችሁ የምችለው ተመሳሳይ ነገር ተፈረወርቅ፡ በትሩና ዘውገ ግብረአበሮቻቸው ግርማ ንጉሴ ለእናንተ እንዳሉት ሁሉ ላልደወሉልኝም ማለታቸው አይቀሬ ስለሆነ ሕዝቡን በማክበር ከዚህ በታች ያለውን መግለጫ ባጭሩ አቀርባለሁ ሰፋ አድረጌ ግን ሃቁን ከነማስረጃው አቀርባለሁኝ እንዳስፈላጊነቱ በቅርብ።
እነዚህ ግለሰቦች እንደሩ እንዲኖር በትክክሉ የማይፈልጉ ናቸው። ከአዲስ አበባም በሃምሳ ሁለት ገጽ የቀረበላቸው መመሪያ በዚህ መልክ በእየ ድርጅቱና ሕዝቡ በሚሰባሰብበት እየገቡ ሕዝብን መበታተን ስለሆነ እነ ዚህ ግለሰቦች ደሞዝ ከኤንባሲው የሚያገኙበትን ስራቸውን እየሰሩ ነው ያሉት ቁዋሚ ስራቸው ሕዝቡን በውጪ ያለውን የትግሬ ነጻ አውጪ የኢትዮጵያን ሕዝብ በክልል ከፋፋዩን አላማ ማስፈጸም ስለሆነ ይሄንንም ወደ ፊት በዚሁ ብሎግ በከፊል እየተደረገ ይወጣል ታዩታላችሁ ለማታውቁት ማለት ነው እንጂ ብዙ ወገን ያነበበው ነው። ጥሩ ምሳሌ በትሩ የመለስ መልክተኞች በመጡ ጊዜ ሆነ ብሎ እስሙም እንደሱው በስውር በድርጅት ስም የሚንቀሳቀሱት ጭምር የተጫወቱትን ቲያትር አንዱ የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው። ግንቦት ሰባት በትሩ የገባውም ግንቦት ሰባት የሚለውን የማፈራረሻ ዘዴ ለማጥናት ነው ያለውን ክፍተት።
እድሩን እነዚህ  ግለሰቦች እንዳይቁዋቁዋም በድብቅ ስብሰባ እያደረጉ ስማቸውን ሳያስቀመጡ ወረቀት ሲበትኑና በየዋህ ሰዎች ነገሩ ባልገባቸው በጊዜው በእውነት የጋራ ማረዳጃ ማሕበሩን ለማዳንና በእድር እንዳይተካ ታሰቦ መስልዋቸውና ቀባሪ ለሌለው መረዳጃ ማሕበሩ መቅበሪያ እንዲሆን በማሰብ በግርማ ንጉሴ አማካኝነት ይሰራጭ የነበረውን አንዴ ኮሚኒቲ ፎር ሴል በሌላ ጊዜ ማር የተለወሰ መርዝ ወዘተ በሚል በኤርፓርት ሳይቀር በስብሰባ እያሳተፋቸው አሳምኖ በሰጣቸው መሰረት አምነው ተቀብለው በግልጽ ቤተክርስቲያንና ታክሲ ወይም ኤርፓርት ጭምር ሲበትኑ ነበር። እንደውም አቶ ንጉሴን እድሩ እንዲቁዋቁዋም በጣም ይጥሩ ከነበሩ ታክሲ ነጂዎች ጋር መጣላታቸው ግልጽ ነው። ይሄ  ሁሉም ያየው ሲሆን ለዚህም መሳሪያ ካደረግዋቸው መሃል በጣም ሰው ሲቸገር እሮጦ የሚደርሰውን አቶ ንጉሴ ጋረድንና ወይዘሮ ቲና ካሳይን መጥቀስ ይቻላል ለማለት ነው።
ሆኖም የሚበተነው ወረቀት ላይ ለሕብረተሰቡ ተቆርቁዋሪዎች በሚል ብቻ በማስቀመጣቸው ወይዘሮ ቲናም ሰዎችን ስለምትረዳን አቶ ንጉሴም በቤተክርስቲያኑም ቢሆን አገልጋይ በመሆኑ ም እመናኑ የግራማ ንጉሴና የዘውገ ፡ የአመሃ መልክት በሚገባ ሲተላለፍ እነሱ ቆመው ያዩ ነበር ለሕዝቡ ለመሰራጨቱ ግባቸው። ከናካቴው እነሱ እራሳቸው ጉዳዩን እንደማያውቁ ሲቀበሉም ነበር።
በሚስጥር በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ ሴንትራል ኤክስፕሬስና ሮያል ቲንሺ ጽህፈት ቤት ውስጥ  እኔም በስብሰባቸው ላይ ተገኝቼ ተንኮላቸውን አየሁት።
 አመሃ የተባለው የቦረድ አባል ማለትም እራሱን ዶክተር አመሃ ነኝ በሚል ዶክተር ሆኖ የማይስራ  አንዱ እድሩ እንዳይቁዋቁዋም አድፋጭ ህዝቡን ለመከፋፍል የመከፋፈያ የነገር ደማሚት ቀባሪዎች መሃል ሲሆን አገሬ ኢትዮጵያም ይሄንን ስለሚያውቅ ከዛም መረዳት ይቻላል። ሆኖም እድሩን ለእድሩ የተነሱት ሲያድኑት፡እኔ ደግሞ የመረዳጃ ማሕበሩንና የሬዲዮን ስርጭቱን ከመነጠቅና ወደ ግል ጥቅም ለአዲስ አበባው መንግስት መሳሪያ እንዳይሆን አድኛለሁ በጊዜው።  የእነሱ እኔን ሬዲዮን አዘጋጅ፡ ቴረሪስት ብላ የመረዳጃ ማሕበሩና እኛን ከሰሰችን የክስ ወረቀት ደርሶናል ድረሱልን ብሎ በውሸት መብረቅ መተርከክና የጋራ መረዳጃ ማህበሩን በእነሱ አነጋገር ኮሚኒቲውን ልታፈርስ ነው ብለው በቡዋረቁት ጉዳዩ የሞተ ወይም ለፍርድ ቤትም ጊዜው ያለፈበት ቢመስላቸውም፡ ሃቁ ሃቅ ስለሆነ በሆቴል ካንጋሩ ፍርድ ቤት ስብሰብ እኔን ለመጉዳት አርባ ሰዎች ኮሚቲ ብለው ፈጥረው ቢዋዥቁም ፍንክቺም አላልኩኝም። ለዚሁም ባለፈው እሁድ በጁላይ ሃያ አራት በመረዳጃ ማሕበሩ ጥሪ በተደረገው ሕዝባዊ ስብሰባ ተገኝቼ መረዳጃ ማሕበሩን ለሁለት የድብቅ አላማቸው አፍርሰውት እንደነበረና በሁለትሺ ሰባት እነዚህ በእኔ ላይ የትግሬ ነጻ አውጪ ተቀጣሪዎች ያወረዱት ውርጂብኝና ፍረጃ ፡  መረዳጃ ማህበሩንና ሬዲዮኑን ልታዘጋ ያሉት ውሸት መሆኑን ገልጬ ሰነዱን መረዳጃው በኦገስት ሃያዘጠኝ ሁለትሺ ሰባት ፈርሶ መስከረም አስራ አምስት ቀን ሁለትሺ ስምንት ማለትም እኔላይ ያንን ሁሉ ወርጅብኝ ባወረዱና ፈረድንባት በጠቅላላ ጉባኤ ባሉ በዘጠንኛው ወር ወደው ሳይሆን ያሰቡትን አላማ እነሱም ይሁኑ የትግሬ ነጻ አውጪ ተፈጻሚ እንዳያደርጉት በማድረጌ ሳይወዱ በግድ ሪንስቴት ወይም መልሶ መረዳጃ ማሕበሩ ሕጋዊነቱና እንዲያገኝ በስቴት ኦፍ ቴክሳስ ያደረኩበትን በስብሰባው አዳራሽ በተሰበሰበው ሕዝብ ፊት ለአዲሱ ቦርድ አባላት አስረክቤለሁ።
ፍሮድ ሰርቶ በመኖር የሚታወቁት ከእነ ደጋፊዎቻቸው ጭምር ባሉበት ሳስረክብ ጪጭ ከማለት ሌላ አንዲትም ቃል ያለመተንፈሳቸውን ከቦርዱና እራሳቸውን ሲክቡዋቸው ከነበሩት መስማት ይቻላል። የሬዲዮን ስርጭቱም እንዳላዘጋሁኝ ሽንጤን ገትሬ ተናግሬአለሁ። ተፍራወርቅንም የመረዳጃ ማሕብሩን ገንዘብ በፍሮድ እንደበላው ከእነ ግብረአበሮቹ ሕዝብ ፊት ለማንም አንገቴን ሳልደፋ ተናግሬአለሁ 
የታደረከው ገንዘቡን? ብዬም ጠይቄአለሁኝ።
በመጨረሻም ለዛሬ ለጥያቄያችሁ ይረዳ ዘንድ፡
እኔ ሳልሆን መረዳጃ ማሕበሩ ከእድሩ ጋር እንዳልሆነ መልስ የሰጠው
በስብሰባው ላይ በእድርተኛ ለቅረበልት ጥያቄ የእድሩ ሊቀመንበር ነው የተባለው ነው።  ስለ እድሩ ልጠየቅም ለመልስም አልችልም እድሩ ውስጥ የለሁበትም እስከዛሬ ስለ እድሩ ምንም አይነት ጥያቄ ኖሮኝም አላውቅም ስለመረዳጃ ማሕበሩ ብቻ እንጂ። እድሩ እንዲቁዋቁዋም ከመደገፍ ሌላ አይቁዋቁዋም ብዬም አላውቅም መክኒያቱም ማንም እድር ማቁዋቁዋም መብቱ ነው። እኔም እድር የማቋቁዋም መብት እንዳለኝ ሁሉ።
ሲበተን ስለነበረው ወረቀትና ለምን እድሩ እንዳይቁዋቁዋም እንደጣሩ በጊዜው፡ ከዛም  እንዴት እድሩን ለይስሙላ ብቻ በመረዳጃ ማሕበሩ ስር ነው እያሉ ፍሮድ እየሰሩ እድርተኛውም ሕብረተሰቡም ሳያውቅ እስከወጡ ድረስ እንደኖሩ ማለትም አንድም ሰው ሳይረዱበት ገንዘቡ ሙልጭ ብሎ ሃምሳ አራት ሺው የራሱ የመርዳጃ ማሕበሩ እድሩ ሳጀመር በፊት ያለውን ጭምሮ ገንዘብ ከካቶሊክ ቻሪቲ ተሰጠን ያሉት ጭምር ያለወጪ እንደጠፋና ከትግሬ ነጻ አውጪ መግስት ሃምሳ ሁለት ገጽ መመሪያ ይዘው በመሃላችን ኢንፎርሜሽናችንን እያወጡ ከእድሩ የሚገኘውን ጭምር አደጋ ላይ ሕዝቡን እንዳጋለጡት ሰፋ አድርጌ ስለምጽፍ ለዛሬ ግን እድርተኛው መሳሪያቸውና ማስፈራሪያቸው አድርገውት ሕዝቡን ሰላም እንዳያገኝ እየተጠቀሙበት ስለሆነ
እድርተኛው እንዲጠነቀቅ አሳስብለሁ። እድርተኛውም ለእድሩ ችግር ፈጣሪዎች ናቸው በሚል ስለሚነጋራቸው ሰዎች እየደወሉ ችግራችሁ ምንድነው? ብለው ቢጠይቁ አንድም ሰው እድሩን እንደማይቃወምና የማንም ጉዳይ እንዳልሆነም ይረዱታል። በዚህ አይነት መንገድ ብቻ ነው ሰላማቸውን ሊያገኙና ሁላችንም የእድሩ አባላት ልንሆን የምንችለው።
እድርተኛውን በዛሬው ስብሰባ በሚካኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ለማበጣበጥና ሃሰትም ለማስተጋባት እንደተዘጋጁ ከላይ እንደገለጽኩት ጥያቄ የጠየቁኝ ወገኖቼ ባሰረዱኝ መሰረት ደርሼበታለሁ። እነዚህ ሰዎች አልቆላቸዋል መረዳጃ ማሕበሩን በሚመለከት ነገር ግን እድሩን ለመቆጣጣርና ግባቸውን ለመምታት የማይፈነቅሉት ድንጋይ ስለሌለ እድርተኞቹ እድር ውስጥ ካልገባው ወደ ሰላሳሺ ከሚሆነውም ወገን ጋር መጋጨት እንዳይሆንባቸው እላለሁ።
 እኔን በሚመለከት እድርተኛው በማንኛውም ጊዜና ሰአት ቀደም ብሎ ነግሮኝ ስብሰባ ቢጠራኝ እራሳቸው ሌቦቹ ባሉበት ለማስረዳት ዝግጁ ስለሆንኩኝ ችግር የለውም። እድሩን የምደግፍ መሆኔን ደጋግሜ እንደገልጽኩት አሁንም በድጋሚ እደገና ማረጋገጥ እወዳለሁ። በጁን አምስት በዴኒስ ሬስቶራንት ለኢትዮጵያ ቀን ዝግጅትን አስመልክቶ በተጠራው ስብሰባ በተገኘሁበት የእድሩ ጸሃፊ እየሰማ እድሩን እስከ ሶስትሺ ብሎም አምስትሺ ድረስ ባጭር ጊዜ እንዴት ልናደርሰው እንደምንችልና ሕግን በማይንጻረር መንገድ ሕብረተሰቡንም አደጋ ላይ በማይጥል እድርተኛውንም መረዳጃ ማሕበሩንም በሚረዳ መልኩ ሊሰራ እንደሚቻል  በስብሰባ አነጋግሩኝ ማለቴም እድሩን ስለምደግፍ ነው። እድሩን የምቃወም ቢሆን እቃወማለሁ እላለሁ ስለማልቃወም ግን ትቃውማለች እያሉ አጀንዳ በእድር ለማስያዝ መርዋርዋጥ ግን የእኔን ስም እየተጠቀሙ እድሩን ልክ ባልፈው እሁድ መረዳጃ ማሕበሩን አዲስ ቦርድ በእድርተኞቹ በመጠቀም አውርዶ በቁጥጥራቸው ስር ለማድረግ እንደጣሩትና እንደከሸፈባቸው እድሩን በቁጥጥራቸው ስር ለመመለስ የሚያደርጊት ጥረት ነው። እኔ ሳልጠየቅ መልስ ሳልሰጥ አንድ ቃል ይዞ መሳሪያ የሚሆኑ ሰዎች የሐረርወርቅ ይሄን አለች ያን አለች ፡
ወሬ አናፋሽነታቸውን እንጂ ወንድነታቸውን አይደለም የሚገልጹት እድሩን በሚገባ የምደግፍ መሆኔን በድጋሚ በተደጋጋሚ እገልጻለሁ። ጊዜ ወስዳችሁ መወናበድ ስልችቶዋቸው ለደወላችሁልኝ ትልቅ ምስጋና አቅርባለሁ። ወሬ አናፋሹም እንደእናንተ ልብ ኖሮት ጠይቆ መረዳትን እንዲማር እጸልይለታለሁ።

 ላንባቢያንም ከምስጋና ጋር ፡
የኢትዮጵያወርቅ (የሐረርወርቅ) ጋሻው።
 ዘብሄረ አንድ ኢትዮጵያ አንድ ሰንደቅ አላማ አንድ ሕዝብ።

Tuesday, July 26, 2011

"የኢትዮጵያ ቀን 2011 በዳላስቴክሳስ አዘጋጅ ኮሚቲ"

"Ethiopian Day 2011 Organizing Committee"
     Yeharerwerk Gashaw
         Chairperson
  


        ይችን ጥሩ ቀን ለፈቀደልን ምስጋና ለሁሉም ስልጣንና ወሳኝነት ላለው ለልኡል እግዚአብሄር ይሁን። አሜን። 
 
ዛሬ የቅዱስ ገብረኤል ቀን ነው። መልካም የገብረኤልቀን ያድርግልን።

አንባቢያንና ለኢትዮጵያ ቀን እንድናገለግል የመረጣችሁን በጠየቃችሁን መሰረት ባጭር ጊዜ ውስጥ ያከናወንናቸውን እነሆ።
በጁን አምስት ማለትም አንድ ወር ሃያአንድ ቀን ሆነው ማለት ነው የኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበር ቦርድ በይፋ ለዚህ አመት የኢትዮጵያ ቀን በአል አዘጋጅ ኮሚቲ  ለማስመረጥ በጠራው ስብሰባ ላይ ጥሪ አክብረን በቦታው ተገኝተን በመጨረሻም ሰባት ሰዎች ተመርጠን ሁለቱ ወንድሞች በስብሰባ ባይሳተፉም አምስት የቀረንው የሰራንውን ኢሜል እያደረግንላቸው ካስታወቅን በሁዋላ አንዱ የስብሰባው ቀን ይቀየርልኝ ባሉት መሰረት ብንቀይርም ከተመረጥን በሁዋላ አንድም ስብሰባ ላይ ሳይገኙ ቀርተዋል። ሌላው ቀደም ሲል በደረሰባቸው አደጋ መክኒያት ከኮሚቲው ጋር ለመስራት በየጊዜው በስብሰባ ለመገኘት  እንደማይችሉ ገልጸዋል። ሁለቱም ከኮሚቲው ለቀናል የሚል ደብድቤ ግን አልጻፉልንም። ሆኖም አምስት የኮሚቲ አባል ስራውን ስራውን ባጭር ጊዜ ለቦርዱ አቅርበናል። ተጨማሪ አስራ አምስት ሰዎችና ሰላሳ ልጆችም መዝግበን ለመጨመርም እየስራን ነው።

-----Original Message-----
From: yehar9 <yehar9@aim.com>
To: sesaxy <sesaxy@gmail.com>
Sent: Mon, Jun 13, 2011 6:16 pm
Subject: Ethiopian Day 2011 Organizing Committee meeting out come report to MAAEC

የዚህ አመት የኢትዮጵያ ቀን "የኢትዮጵያ ወጣቶች በአል" ብለንዋል። ወጣቱ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን አዘጋጅ ኮሚቲውን በሙሉ የሚመራው አድርገን አዘጋጅተንዋል። ፊልም ፕሮዲስሮችና ዳሬክተሮች "ዳላስ" የሚለውን በአለም የታወቀውን የቴሌቪዢን ሾው የሰሩ ሳይቀሩ ልጆቹን እድል ይሰጣሉ ለሁለት ሳምንት ኦገስት ውስጥ። ልጆቻችን ከእኛ ሕብረተሰብ ወጣ ብለው ብዙ ነገሮች ላይ ሊያሳትፍቸው የሚችል በር ልንከፍትላቸው ይገባል!
Ethiopian Day 2011 Organizing Committee
Dallas, Texas
በአቶ ስዩም የሕዝብ ግንኙነት አማካኝነት
ይድረስ ለኢትዮጵያ መረዳጃ ማሕበር በዳላስ ፎርት ወርዝ።

June13,2011

Subjec፡ meeting and out come report. ስብሰባችንና ውጤቱ ከአጭር ማሳሰቢያ ጋር በማጣመር.

በመጀመሪያ ትልቅ ሰላምታና ምስጋና ለኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበር አስተዳደር ስናቀርብ ከአክብሮት ጋር ነው። እኛንም አስመርጣችሁ ሃልፊነቱና ይሰራሉ ብላችሁ እምነቱንም ስለጣላችሁበን ስለ እምንታችሁ በጣም እናመሰግናለን። ስራውንም እራሳችን ሰርተን ማንም ከሁዋላ ልብሳችንን ይዞ በዚህ ሂዱ በዛ ስሩ ሳይለን ችሎታችንንና አስተዋጽዎቻችንንም ታማኝነትን ለሕዝቡ ጥቅም ብቻ የተራብን መሆናችንን ጭምር የምናሳይበት በነጻነት የምንሰራበት መድረክ ስለሰጣችሁን በዚህ በዳላስ ፎርት ወርዝ አንድነቱንና ሰላምን አጥቶ በየት የአንድነት ሜዳ እንደሚገናኝ ግራ የገባው ወገን ስምና በራሳችንም እያመሰገነን ይሂንን ቀጥተኛ አሰራራችሁን በማጠናከር ቀጥላችሁ ወደ ፊትም በከተማው ለሚኖረው ሕዝባችን ጥሩ አራአያ ሆናችሁ የአንድነትና የኢትዮጵያዊነት የጨዋ ጸባይን የጠፋውን በተለያየ መልኩ የክብር ችቦ አብርታችሁ በዳላስ ከተማ ላለው ወጣት እንደምታስረክቡ ተስፋ ጥለንባችሁዋል።
  የትናንትናው ጁን አስራ ሁለት ስብሰባና ውጤቱ ባጭሩ፡
ትናንትና ባደረግንው ስብሰባ በጣም ጥሩ ውጤት አምጥተናል። ተነድፈው በቀረቡት አሳራ ሃንድ የተግባር ኮሚቲ ላይ ስለ እያንዳንዱ የኮሚቲ ተግባርና ምን ያህል ሰው ለእያንዳንዱ ተግባር ማከናወኛ እንደሚያስፈልግ ጭምር ተነጋግረን ቀጥሎም በሻለቃ ሱራፌል የቀረበውን የሽልማት ኮሚቲ በአስራ ሁለተኛ ኮሚቲነት አስቀምጠንዋል። ለእያንዳንዱም የተግባር ስራ አምስት አምስት ሰው ልንመድብ ተስማምተናል። ለዚሁም እያንዳንዳችን አስር አስር ሰው መልምለን በሚቀጥለው ስብሰባ ካሳተፍን በሁዋላ እያንዳንዱ በበጎ ፍቃድ ተሳታፊ ምን ያህል ሰአት በቦታው ላይ እንደሚቆይ እና በእየ ሁለት ሰአቱ ወይም መቀያየር እንዳለበት ጭምር ወስነናል። አምስት ሰው ጠዋት አምስት ሰው ከሰአት አምስት ሰው ማታ እንደ ማለት ነው። ይሄውም ሁሉም የበአሉ ደስታ ተቁዋዳሽ እንዲሆን ሲሆን ከእነ ቤተሰቡ በአስተናጋጅነት ብቻ አይሰማውም በነገራችን ላይ ፡ የዚህ አይነት አስራር የተለምደ አልነበረም በመረዳጃ ማሕበሩ።የበአሉን ዝግጅት በተራ ተከተል ይሄውም ከመጀመሪያው ቀን መክፈቻ እስከ መዝጊያው ያለውን በዝርዝር በተራ ተከተል ለማቅረብ የእናነተ ሃሳብ መጨመር ስላለበት ከዚህ በታች ባስቀመጥነው ኮሚቶዎች ላይ የሚጨመር ኮሚቲ ካለ ጨምራችሁ እንድትልኩልን በኢሜል ወይም፡ ባለው እኛ የዝግጅቱ ኮሚ የተስማማንበትን ኮሚቲ ተስማምተናል ካልችሁም መልሳችሁን በዚህ ሳምንት መጨረሻ ድረስ ማለትም በጁን አስራ ስምንትና አስራ ዘጠኝ ድረስ ካስታወቃችሁን በኛ በኩል የኢትዮጵያን ቀን አስረኛ አመት ዝግጅት አጠናቀን ስራውን ለመጀመር በተግባር ይረዳ ዘንድ ልናቀርብላችሁ ዝግጁነን። ይሄንን ስንል የበአሉ አዘጋጅ ኮሚቲ እንደሚያስበውና እንደተዘጋጀ ከሆነ በጁን መጨረሻ ለእስፓንሰር ደብዳቤ መላክና በነብስም በቦታው በመገኘት እርዳታ የሚያበረክቱ ድርጅቶችን ጭምር ማነጋገር የምንጀምርበት ይሆናል። ማለትም ጁላይ ገንዘብና እርዳታ የምናገኝበት መጀመሪያው ሲሆን ከዛም ጎን በአሉንና ተሳታፊዎችንም ሕዝቡንም የምናነጋግረበት ይሆናል።
ቦታ ቶሎ መያዙ እስፓንሰር ለማብዛት ስለሚያስችለን በተለይ ፌር ፓርክ ቢደረግ በአሉ ይሄ ለአስራ አምስት አመት ከአሜሪካን ሕብረተሰብና ከውጪው እንዳይገናኝ ተደርጎ የኖረው የኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበር ልቆ የሚታይበትና ለምሳሌ ታክሲ ነጂዎቹን ብንወስድ ሕብረተሰባችን በመረዳጃ ማሕበሩ ስም በብዙ መልኩ በከተማው ከመንግስት መስሪያ ቤት እከ እያንዳንዱ የዳላስ ፎርት ወርዝ ህብረተሰብ እንዲሳተፍ በማድረግ ትልቅ ስም ይሰጠን የነበረውን አጥቶ ታክሲ ነጂው ሲቸገር አንድ የመረዳጃ ማሕበር የታወቀ ባለመኖሩ ነበር በአሜሪካን ጋዜጠኞችና በሕዝብ ተመርጠው ስልጣን በጨበጡት በኩል ድምጽ ልናሰማ ሃይል የምንሆን ኢትዮጵያውያን ተፈልገን የተጠራንውና ያስተጋባንው። ታዲያ አንድ ታዋቂ ኢትዮጵያዊት ይልቅ የኢትዮጵያ የጋራ መረዳጃ ማሕበርና ታዋቂ ቢሆን በበለጠ ክብር የለውም? ይሄን ለማድረግ እጃችሁ ላይ ነው ውሳኔው ወገኖች። ስለዚህ በየስርቻው በቀን አምስት ሺ እየተከፈለ ምንም ለውጥ ለሕብረተሰቡ በማያመጣ ስርቻ ሲደረግ የነበርው የኢትዮጵያ ቀን መንግስት በሚያስተዳድረው ፌር ፓርክ ቢደረግ ብዙ ጥቅም አለው። ለምን ታንክስ ጊቪንግ ይደረጋል የሚሉት እራስ ወዳዶችንም ቢሆኑ ያልደፈሩት ለኢትዮጵያውያን አኩሪ ቦታና ባንዴ ስማችንን ክብራችንን የምናስመዘግብበት ቦታና በአል ነው ፌር ፓርክ ማድረጉ። ቶሎ ከወሰናችሁ በዛሪና በነገው ውስጥ እስፓንሰር ላይ ብቻ ነው ሁላችንም የምናቶክረው ፌር ፓርክ ከሆነ ማንም ኮርፓሬሽን እስፓንሰር ያደርጋል። የበአል ዝግጅት ቦታና የሕብረተሰቡን ብዛት ስለሆነ የምንሸጠው ለእስፓንሰሮች በድጋሚ በተደጋጋሚ ፊር ፓርክ የኢትዮጵያ ቀን የአስረኛው  በአል ቦታ ቢሆን ይመረጣል። ለምሳሌ የከተማውን ከንቲባና አማካሪ፡ የአሜሪካን ምክር ቤት አባላትንና ዳኞችን የኢሚግሬሽን ዳሬክተርንና ታዋቂ የሰው ልጅ መብት ተከራካሪዎችን ጭምር ብሎም እንደ ጄሪ ጆንስ የዳላስ ካው ቦይ ባለቤትን ብሎም ተጫዋቾቹን ለመጋበዝ ቦታው የመጀመሪያው ጥያቄ ይሆናል። አስቡበት በዚህ ዝግጅት ገንዘብ ከውጪው ድርጅቶች ለማግኘት መሆን ይኖርበታል አላማችን። መልሳችሁን የምንጠብቀው በቅርብ የኢትይጵያ ቀን አዘጋጅ ኮሚቴ።
ከአክብሮት ጋር በኮሚቲው ስም፣
የኢትዮጵያወርቅ (የሐረርወርቅ) ጋሻው።
ሊቀመንበር።
ከሕብረተሰቡ ገንቢ አስተያያት ከተሰጡት ሁለቱን ብቻ፡
ለብዙ አመት የኢትዮጵያ ቀን በአል ቀኑ ሲደርስ ኑና ስሩ በሚል ብቻ እየተጠሩ ሲያገለግሉና እንደ ቆሻሻ ወረቀት ሲጣሉ ተረስተው ነገር ግን አመቱ እንደገና ሲመጣ ብቻ የሚታወሱት ከዚህ በታች የሰጡትን አስተያየት እነሆ፡
በቀኑ ከእኛ ጋር ከተሰበሰቡት "አሁን በስብሰባው ተገኝቼ ካገኘሁት በተግባር መምጣቴን ተደሰትኩበት። መክኒያቱም ምንም እንክዋን ለብዙ አመት ለኢትዮጵያ ቀን በበጎ ፍቃድ ሳገለግል ብቆይም አንድም ቀን እንደዚህ እንደዛሬው ስብሰባ ተጠርቼ ገንቢ ሃሳብንና ለሕብረተሰቡ የሚጠቅመውንና የማያስፈልጉና የማያስፈልጉ ተግባሮች ላይ ህሳብ ስጥቼ የእኔም ሃሳብ በበአሉ ዝግጅት ውስጥ ገብቶ ስራ ላይ ውሎ ላይ ይቅርና ምን ታሰባለህ ብሎ እንክዋን አክብሮ ጠይቆኝ የሚያውቅ አንድም የመረዳጃ ማሕበሩ አባል አልነበረም። ዛሬ ግን በተሰጠኝ ያገባህልና ምከርበት በዝግጅቱ ተብዬ ሃሳቤን ለመስጠት በመቻሌ የኢትዮጵያ ቀን በአል አዘጋጅና የመረዳጃው ማሕበርም ባለቤትነት ስሜት እንዲኖረኝ አድርጋችሁኛል ስለሆነም ለመረጡዋችሁና ላስመረጣችሁ ለመረዳጃ ማሕበራችን አዲስ ተመራጮች ንገሩልኝ" ብለው ላለፈው ስድስት አመት ከተካፈሉት የኢትዮጵያ ቀን በመነሳት መታረም ስላለባቸውና ሌላው ቢቀር ቲኒሽ የምስጋና ደብዳቤ ወይም ሰርተፍኬት እንዲዘጋጅ ጭምር መደረግ ያለበትን በተግባር ኮሚቴ አሰራር ውስጥ እንዲገባ ባቀረቡት የነጻ ሃሳብ መግለጽ በደስታ ተቀብለን መዝግበንዋል።
ሁለት ወጣት ሴቶች ለብዙ አመት በኢትዮጵያ ቀን የተካፈሉት ለቦርዱ እንዲተላለፍ ከጠየቁን፡
እኛ በጣም የሚያሳዝነና በዚህ አመት መካፈል የማንፈልገው አንድ ነገር አለ ይሄውም፡ ልክ የኢትዮጵያ ቀን ሲዳረስ ሁለት ሳምንት ሲቀረው መጥታችሁ ደንሱ እንባላለን በቤተክርስቲያን በኩል። ነገር ግን ምን እኛን እና ጉዋደኞቻችንን እንደሚያስደስተንና ሊሰበስበን እንደሚችል የሚጠይቀን አንድም አላይየም ከእነ ቤተሰቦቻችን ጭምር ሄዱና ተካፈሉ የኢትዮጵያን ቀን በአል ዝግጅት ከመባል ሌላ።  ለምሳሌ ባለፈው አመት የተደረገበት ቦታ እንክዋን መንገድ በደንብ ለማያውቅ ኢትዮጵያዊ ይቅርና ለእኛ ለወጣቶቹ እንክዋን የነበረው ችግር በጣም አሳዝኖናል። እልም ያለ ይሄ ነው ሊባል የማይችል ቦታ አንዴ ስህተት ተደርጎ ከታለፈ ለመመለስ አስቸጋሪ የነበረበት ነው።
አንደኛ ቀረብ ያለና ወጣቱን ድግሞ የሚያሳትፍ ካልሆነ በዛ ላይ ልጆች ሁሉ በሃይማኖት ስም እንድንከፋፈል አድርገዋል ቤተሰቦቻችን ጭምር የመረዳጃውም ተጠሪዎች ፈጽሞ ከወጣቱ ጋር ግንኙነት የሌላቸውና እዛም ስንሄድ ክብር አይሰጡንም ፓሊስም ይጠርብናል አንዳንዲም። እንደዚያ ሳይሆን በደንብ የምታሰባስቡን ከሆነ እንሳተፋለን በተለይ ለሞደሊንግን ኮሜርሻል ፊልም ለመስራትም ስለምንፈልግ እድሉን የሐረርወርቅ እንደምትከፍትልን ካለፈው አፎሚያን ኒኮሎዲያን ላይ ስላየናት እየጉዋጉዋን ነው። እድሉን ያገኘችው በየሐረርውርቅ በተዘጋጀው ሾው መሆኑንና እስኮላርሺም እንዳገኘችው ሁሉ፡በሚል ደመደሙ ገንቢ ሃሳባቸውንና ምኞታቸውን ። 

Ethiopian Day 2011 Organizing Committee
Steering Committees

1.Sponsors/Support Committee
2.Venders/ID Committee

3.Silent Auction

4.Finance/Membership drive Committees

5.Entertainment Committees

6.Souvenir Booklet/Programs

7.Media/Public Relations/Community Relations

8.Children Village

9.Schedule & Super Vising Committee

10.Volunteer & Hospitality Committees Security

11.Guest Coordinating and Feed Back-Task as needed Committee

12. Honoring Committee

Monday, July 11, 2011

Oriental Orthodox Youth Confrerence


By Lielt Samuel,

For those who don’t know, a three day Oriental Orthodox Youth Conference, organized by our own Deacon Andualem, took place at St. Michael Ethiopian Orthodox Tewahedo Debre Meheret St. Michael Church in Garland, Texas this past week (July 7th-9th). Visitors from other oriental orthodox churches around the Dallas area that attended the event included those from St. Thomas Indian Orthodox Church, St. Mary Syrian Orthodox Church, St. Philopateer Coptic Orthodox Church, and St. Mary Ethiopian Orthodox Church. Guest speakers including priests and professors came to preach to the youth from these churches as well as St. Mary Ethiopian Orthodox Church in Los Angeles, and the University of Toronto in Canada.

The first two days of the conference were divided into three sessions daily (according to age) which were composed of lessons, prayer and mezmur, icebreakers and activities for the youth to get to know one another and enjoy, and a grand dinner to finish off the day. On the third day of the conference, for the first time at St. Michael, the divine liturgy was given in English so that all youth attending could understand and take part in the mass.

The youth conference was a great experience! It was refreshing to have an event at church that was centered around the youth, as well as one in which we could meet brothers and sisters in Christ from other Orthodox churches. We learned a lot about the importance of our tradition and religion as well as the similarities in our churches from the wonderful speakers that came to talk to us. The Diving Liturgy being given in English was an outstanding part of the conference that allowed us to really understand the significance and importance of the Kidasse that takes place at our church every Sunday.

I thank Ethiopian Orthodox Tewahedo Debre Meheret St. Michael Church for their great support of the event as well as Deacon Andualem for organizing the conference and always thinking of the youth. I look forward to the youth conference next year being even bigger and even better event!